እዚህ ተደፍቶ የሚለው ፈሊጣዊ አባባል ተመስጦ ማለት ነው፡፡ አት “በአባቱ ላይ ተደፍቶ በሀዘን” (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)
አስከሬንን የሚያስተካክሉ አገልጋዮቹ
መቀባት ከቀብር በፊት አስከሬኑ እንዳይፈርስ የሚያቆዩበት ልዩ መንገድ ነው (ንኀብነት ወይም ለዛ ባለ መንገድ መግለጽን ይመልከቱ)
4ዐ ቀናት ወሰደባቸው (ቁጥሮችን ይመልከቱ)
7ዐ ቀናት (ቁጥሮችን ይመልከቱ)
“የማዘኑ ቀናት” ወይም “ለእርሱ የማልቀስ ቀናት”
እዚህ የፈርዖን ቤት የፈርዖን ንጉሣዊ ፍርድ ቤት ወክል ባለሥልጣናት ያመለክታል ዮሴፍ ለፈርዖን ባለሥልጣናት ተናገረ (ምትክ ቃላት ይመልከቱ)
ሞገስ ማግኘት የሚለው ሐረግ በአንድ ሰው ፊት ተቀባይነትን ማትረፍ የሚናገር ፈሊጣዊ አባባል ነው:: አት “በእናንተ ፊት ሞገስ ካገኘሁ ወይም በእኔ ደስተኞች ከሆናችሁ” (ፈሊጣዊ አባባልና ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ይህ ሁለት ደረጃና ሶስት ደረጃ ጥቅስ ይዞአል እነዚህ በተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊገለጹ ይችላሉ:: አት “በከነዓን ምድር በቆፈረው መቃብር እንዲቀብረው አባቴ በሚሞትበት ጊዜ እንዳመለኝ ለፈርዖን ንገሩልኝ:: አባተን እንዲቀብረውና ከዚያም ተመልሸ እንዲመጣ ፈርዖንን ጠይቁልኝ” (ጥቅሶችን በጥቅስ ውስጥና ቀጥታና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)
ሊሞት ነኝ
ከግብጽ ወደ ከነዓን መጓዝ በሚነገርበት ጊዜ “ወደ ላይ መውጣት” የሚለውን ሀረግ መጠቀም የተለመደ ነው፡፡
የመንግሥት ምክር ቤት አባላት ለፈርዖን ነገሩትና ከዚያም ፈርዖን ለዮሴፍ መለሰ (ግምታዊ እውቀት ወይም ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)
ለእርሱ እንደማልህለት
ከግብጽ ወደ ከነዓን መጓዝ በሚነገርበት ጊዜ “ወደ ላይ መውጣት” የሚለውን ሀረግ መጠቀም የተለመደ ነው፡፡
የፈርዖን ከፍተኛ መሪዎች ሁሉ የቀብሩን ሥነሥርዓት ተካፈሉ (የሁኔቶች ሥርዓት ይመልከቱ)
የፈሪዖን ቤተምንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናትን ያመለክታል
ይህ እንደ አዲስ ዐረፍተ ነገር ሊተረጐም ይችላል:: አት “የግብጽ ምድር ፤ እንዲሁም የዮሴፍ ቤተ ሰዎች ወንድሞቹና የአባቱ ቤተ ሰዎች ከእርሱ ጋር አብረውት ሄዱ” (የሁኔቶች ቅደም ተከተል ይመልከቱ)
እዚህ በሠረገላዎች የተቀመጡ ሰዎችን ያመለክታል (ምትክ ቃላት ይመልከቱ)
እጅግ ብዙ ሰዎች ጉባኤ ነበር
“እነርሱ” የሚለው ቃል በቀብር ሥነሥርዓቱን ይካፈሉ የነበሩ ሰዎችን ያመለክታል
ተገቢ ትርጉሞች 1) “አጣድ” የሚለው ቃል እሾህ ማለት ነው፤ አናም እጅግ ብዙ እሾሆች የሚበቅሉበት መሬት ሊባል ይችላል ወይም 2) “የአውድማው ባለቤት ስም ሊሆን ሊችላል:: (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)
እጅግ መራራና ከፍተኛ ልቅሶ አልቅሰው ነበር
7 ቀን (ቁጥሮችን ይመልከቱ)
ተገቢ ትርጉሞች 1) አጣድ የተባለው ሰው አውድማ ውስጥ ወይም 2) አጣድ በተባለው አውድማ ውስጥ:: (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)
የግብጻዊያን ልቅሶ መራራ ነበር
ተርጓሚዎች የሚከተለውን እንደ ግርጌ ማስታወሻ ሊጠቀሙ ይችላሉ አቤል ምጽራይም የሚለው ስም የግብጻዊያን ሐዘን ማለት ነው (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)
የያዕቆብ ልጆችም
ልክ መመሪያ እንደሰጣቸው
ልጆቹም አስከሬኑን ተሸክመውት
ማክፌላ የቦታ ወይም የግዛት ስም ነው በዘፍጥረት 23፡9 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)
የሔብሮን ከተማ ሌላ ስምዋ ነው በዚያ ይኖር በነበረው በአብርሃም ወዳጅ መምሬ ስም ሳትሰየም አትቀርም፡፡ በዘፍጥረት 13፡ 18 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)
ይህ የወንድ ሰው ስም ነው ኬጢያዊ የኬጥ ዘር ነው በዘፍጥረት 23፡8 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)
ዮሴፍ ወደ ግብጽ ተመለሰ
አብረውት የሄዱት ሁሉ
እዚህ ቂም ዮሴፍ በእጁ እንደምይዝ ዕቃ ተደርጐ ተገልጾአል አት ምናልባት ዮሴፍ የጠላን ይሆናል (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
እርሱን የበደለውን ሰው መበቀል አንድ ሰው ከሌላ ሰው የተበደረውን እንደመመለስ ተደርጐ ተገልጾአል:: አት “ባደረግንበት ክፋት ምናልባት ልበቀለን ይችላል” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ይህ ሁለት ደረጃና ሶስት ደረጃ ጥቅስ ይዞአል እንደተዘዋዋሪ ጥቅስም ሊገለጹ ይችላሉ:: አት “አባትህ ከመሞቱ በፊት እኛ የበደልንህን ይቅር እንዲትለን እንድንነግርህ አዝዞናል” (ጥቅስን በጥቅስ ውስጥ እና ቀጥተኛና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)
ያዕቆብ ለወንድማማቾች ሁሉ አባት ነው:: እዚህ ዮሴፍ አባቱ ለተናገረው ትኩረት እንዲሰጥ “አባትህ” ብለው ይናገራሉ:: አት “አባታችን ከመሞቱ በፊት”
በአንተ ላይ ስላደረጉት ክፉ ነገሮች
ይህ በዚህን ጊዜ ማለት አይደለም ነገር ግን ለሚቀጥለው ዋና ነጥብ ትኩረት እንዲሰጥበት ነው
ወንድሞቹ ራሳቸውን “የአባትህ አምላክ ባሪያዎች” ብለው ይገልጻሉ:: (አንደኛ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)
የሴፍ ይህን መልእክት በሰማ ጊዜ አለቀሰ
በፊቱ ወደ መሬት ጐንበስ በማለት ሰግደው፤ ይህ የትህትና እና ለዮሴፍ ክብርን የመስጠት ምልክት ነው፡፡ (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)
ዮሴፍ ወንድሞቹን ለማደፋፈር ጥያቄ ይጠቀማል:: አት “እኔ በእግዚአብሔር ፋንታ አይደለሁም” ወይም “እኔ እግዚአብሔር አይደለሁም” (አግናኝ ወይም ሽንገላ አዘል ጥያቄዎችን ይመልከቱ)
እናንተ ክፉ ነገር አድርጋችሁብኝ
እግዚአብሔር ለመልካም አደረገው
ስለዚህ እኔን አተፍሩ
ሁል ጊዜ እናንተና ልጆቻችሁ በቂ ምግብ እንዲኖራችሁ አረጋግጣለሁ
እዚህ ልቦች ወንድሞቹን ያመለክታሉ:: አት “አጽናናቸውም ደስም አሰኛቸው” (ክፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን እንደ ክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
11ዐ ዓመት (ቁጥሮችን ይመልከቱ)
የኤፍሬም ልጆችና የልጅ ልጆች
ይህ የዮሴፍ ወንድ የልጅ ልጅ ስም ነው (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)
ይህ አባበል ዮሴፍ እነዚህን የማኪርን ልጆች የራሱ የልጅ ልጆች አድርጐ ተቀበላቸው ማለት ነው:: ይህም ዮሴፍን ለመውረስ ልዩ መብት አላቸው ማለት ነው (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)
በዘፍጥረት 5ዐ: 24./26 “እናንተ” የሚለው ቃል የዮሴፍን ወንድሞች ነገር ግን ደግሞ የእነርሱን ልጆች ያመለክታል፡: (ምትክ ቃላት አጠቃቀም ይመልከቱ)
ከግብጽ ወደ ከነዓን መጓዝ በሚነገርበት ጊዜ “ወደ ላይ መውጣት” የሚለውን ቃለ መጠቀም የተለመደ ነው:: አት “ከዚህ ምድር ያወጣችኋል ወደ ምድራችሁ ይወስዳችኋል” (የክስተቶች ቅደም ተከተል ይመልከቱ)
መቶ አሥር ዓመታት
አንድን አስከሬን ከመቀበሩ በፊት እንዳይፈርስ ለማቆየት መድሃኒት መቀባት ልዩ የሆነ መንገድ ነበር በዘፍጥረት 5ዐ 1 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ
ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል፡፡ አት “አኖሩት” (ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)
“በሬሳ ሳጥን” ወይም “በሳጥን” ይህ ሳጥን የሞተ ሰው የሚቀመጥበት ነው::