ይህ ያዕቆብ ልጆቹን የሚባርከውን መጨረሻውን በረከት የጀምራል:: ይህም እስከ ዘፍጥረት 49:27 ይቀጥላል የያዕቆብ ምርቃቶች በግጥም መልክ ተጽፈዋል (ሥነ ግጥሞችን ይመልከቱ)
ሁለቱ ዐረፍተ ነገሮች ትኩረት ለመስጠት ተመሣሣይ ሃሳብ ይናገራሉ አት ወደ አባታችሁ ኑና በጥንቃቄ አድምጡ (ተመሣሣይ ተነጻጻሪ ይመልከቱ)
ያዕቆብ ራሱን እንደሶስተኛ ወገን ሰው ያቀርባል እንደአንደኛ ወገን ሰው ሊገለጽ ይችላል አት ልጆች ሆይ እኔን አባታችሁን ስሙ (አንደኛ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ወገን ሰው አጠቃቀም ይመልከቱ)
የበኩር ልጄ ኃይሌ የጉብዝናዬ መጀመሪያ የሚሉ ሀረጐች ተመሣሣይ ትርጉም አላቸው ኃይል እና ጉብዝና የሚሉ ቃሎች የያዕቆብ ልጅ የመውለድ አቅሙን ያመለክታሉ በኩር እና መጀመሪያ የሚሉ ቃላት ሮቤል በኩር ልጁ እንደሆነ ይገልጻሉ (ተመሣሣይ ተነጻጻሪ ይመልከቱ)
ይህ እንደ አድስ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል አት በክብርና በኃይል የመጀመሪያ ትሆናለህ ወይም በክብርና በኃይል ማንኛውንም ሰው ትበልጣለህ
ያዕቆብ ሮቤል ቁጣውን እንደማይችል ለማተኮር በከባድ ማዕበል እንደሚዋልል ውሃ አድርጐ ያቀርበዋልና እርሱ የተረጋጋ አይደለም (ተመሣሣይ አባባል ይመልከቱ)
በወንድሞችህ መካከል የመጀመሪያ ወይም አለቃ አትሆንም
እዚህ መኝታና አልጋ የያዕቆብን ቁባት ባላን ያመለክታሉ ያዕቆብ ሮቤል ከባላ ጋር የተኛበትን ያመለክታል (ዘፍጥረት 35:22 ይመልከቱ) አት “ወደ አልጋዬ ስለወጣህና በቁባቴ ከባላ ጋር ስለተኛህ አዋርደህኛልና” (ምትክ ቃላት አጠቃቀም ይመልከቱ)
ሁለቱም ዐረፍተ ነገሮች ተመሣሣይ ትርጉም አላቸው (ተመሣሣይ ተነጻጻሪ ይመልከቱ)
ይህ በትውልድ ወንድሞች መሆናቸውን አይገልጽም ያዕቆብ የሴኬም ሰዎችን ለመግደል አብረው መሥራታቸውን ለማተኮር ነው፡፡
ሰዎችን ለመጉዳትና ለመግደል ሰይፎቻቸውን ይጠቀማሉ
ያዕቆብ ራሱን ለመግለጽ ነፍሴ እና ልቤ የሚሉ ቃሎችን ይጠቀማልና ክፋን ለማድረግ ከሚያቅዱት ጋር ባለመተባበሩ ሌሎች ሰዎችና እግዚአብሔርም ደግሞ እጅግ እንዳከበሩት ይናገራል (ክፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን እንደ ክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
ጉባዔያቸው ውስጥ አልገኝ እነዚህ ሁለቱ ሀረጐች በመሠረቱ ተመሣሣይ ትርጉም አላቸው ያዕቆብ ሁለቱን በማገናኘት በክፉ እቅዳቸው እንደማይሳተፍ አበክሮ ይገልጻል አት ማንኛውንም እቅድ ለማዘጋጀት ከእነርሱ ጋር አልተባበርም (ተመሣሣይ ተነጻጻሪ ይመልከቱ)
ስምዖንና ለዊ ለዕይታ ብለው ቤሬዎችን አስነክሰዋል
ይህ የእንስሳትን ቋንጃ በመቁረጥ እንዳይራመዱ ማድረግ ነው
እግዚአብሔር ስምዖንና ሌዊን የሚረግመው እግዚአብሔር ቁጣቸውንና ንዴታቸውን እንደሚረግም ተደርጐ የገልጾአል:: (ዘይቤያዊ አነጋገርና ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)
አብዛኛውን ጊዜ ነብይ ትንቢትን ሲናገር የሚናገረው ቃል እግዚአብሔር እንደሚናገር ይቆጠራል:: ይህም የሚናገረው ነበዩና እግዚአብሔር እንዴት እንደተቆራኙ ነው::
እረግማለሁ የሚለው ቃል የታወቀ ነው አት ንዴታቸው ጭከናን የተሞላ ስለሆነ እረግማለሁ (የተደበቁትን የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
“እኔ” እግዚአብሔርን ያመለክታል:: “እነርሱ” ስምዖንንና ለዊን ቢሆንም ምትክ ቃል ስለሆነ ለትውልዳቸውም ይሆናል:: “ያዕቆብ”ና “እስራኤል” ተወራራሽ ስሞችና የእስራእል ሕዝብ የሚተኩ ናቸው:: አት ትውልዳቸውን እበትናለሁ በእስራኤልም ሰዎች መካከል አሠራጫለሁ (ምትክ ቃላትና ተመሣሣይ ተነጻጻሪ አባባል ይመልከቱ)
ሁለቱም ዐረፍተ ነገሮች ተመሣሣይ ትርጉም አላቸው (ተመሣሣይ ተነጻጻሪ ይመልከቱ)
ሁለተኛው ዐረፍተ ነገር ለአንደኛው ምክንያት ነው ይህ “ስለ” ወይም “ምክንያቱም/የተነሣ” አገናኝ ቃላትን በመጠቀም ግልጽ ሊሆን ይችላል:: አት “ስለ እጅህ ያመሰግኑሃል” ወይም “ከእጅህ የተነሣ ያመሠግኑሃል” (አገናኝ ቃላት ይመልከቱ)
“ጠላቶችህን ታሸንፋለህ” የሚል አባባል ነው:: (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ለአንድ ሰው እጅ መንሣት ወይም አክብሮት በትህትና ለመግለጽ ጐንበስ ማለትን ይገልጻል (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)
የአንበባ ደቦል እንደሆነ ስለ ይሁዳ ያዕቆብ ይናገራል:: ያዕቆብ የይሁዳን ጥንካሬ በአትኩሮት ይገልጻል:: አት “ይሁዳ እንደ አንበሳ ደቦል ነው” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
“አንተ ልጄ ከአደንህ ተመለስህ”
ያዕቆብ ይሁዳን ከእንስት አንበሳ ጋር ያነጻጽራል አት እንስት አንበሳ በአደን ቀዳማይና ቡድንዋን የሚትከላከል ነች (ተመሣሣይ አባባል ይመልከቱ)
ያዕቆብ ይሁዳ ለሌሎች ሰዎች ምንኛ አስፈሪ እንደሆነ ትኩረት ለመሰጠቅ ጥያቄ ይጠቀማል፡፡ አት “ማንም ሊቀሰቅሰው አይችልም” (አግናኝ ጥያቄ ይመልከቱ)
በትርና ዘንግ ንጉሥ የሚይዛቸው ያገጡ ረጃጅም በትሮች ናቸው የሥልጣን አገዛዝ የሚተኩ ምልክቶች ናቸው እናም ይሁዳ የእርሱን ዘር ይወክላል:: አት “የአገዛዝ ሥልጣን ሁልጊዜም ለይሁዳ ዘር ይሆናል” (ምትክ ቃላትና ተመሣሣይ ተነጻጻሪ አባባል ይመልከቱ)
ተገቢ ትርጉሞች 1 ሰሎ ማለት ክብር ወይም አድናቆት ማለት ነው አት ሕዝቦች እስኪታዘዙለትና እስክያከብሩት ድረስ ወይም 2 ሰሎ የሴሎ ከተማን ይወክላል አት ገዥ ወደ ሰሎ እስኪመጣና ሕዝቦች እስኪታዘዙለት ድረስ ብዙ ሰዎች እንደሚናገሩት ይህ ትንቢት ከዳዊት ዘር ስለሚመጣው መስህ ነው ዳዊት ከይሁዳ ዘር ነውና
ሕዝቦች ሰዎችን ያመለክታሉ አት ሕዝቦች ሁሉ ይታዘዙለታል (ምትክ ቃላት ይመልከቱ)
ሁለቱም አረፍተ ነገሮች ተመሣሣይ ትርጉም አላቸው የወይኑ ፍሬ ብዙ ሰለሆነ አህያው ፍሬዎችን ቢበላ ጌታው እንደማይገደው ተደረጐ ተገልጾአል:: (ተመሣሣይ ተነጻጻሪ እና ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)
የእርሱ ወይም እርሱ በተጠቀሱባቸው ሁሉ ተገቢ ትርጉማቸው 1 የይሁዳን ዘር ያመለክታሉ:: “የእነርሱ” “እነርሱ” ወይም 2) እነርሱ በዘፍጥረት 49:1ዐ ምናልባት ሚናሴን የሚያመለክተውን ገዥ ያመለክታሉ::
ሁለቱም ዐረፍተ ነገሮች ተመሣሣይ ትርጉም አላቸው ይህም በጭማቂዎቻቸው ልብሶቻቸውን ማጠብ እንኳ የሚያስችል ብዙ ወይን ፍሬዎች ይኖራሉ ማለት ነው (ተመሣሣይ ተነጻጻሪ እና ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)
አብዛኛውን ጊዜ ወደፊት የሚፈጸሙ ትንብቶች እንደተፈጸመ ተደርጐ ይገለጻል ይህ በአትኩሮት የሚናገረው ክስተቱ በእርግጥ እንደሚፈጸም ነው አት እነርሱ ያጥባሉ ወይም እርሱ ያጥባል (ወደፊት አመላካች ኃላፊ ክስተት ይመልከቱ)
የወይን ጭማቂን እንደ ወይን ደም ያቀርባል ይህም ጭማቂው ምንኛ ቀይ ቀለም እንዳለው ይገልጻል (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ይህ እንደ ቀይ ቀለም ወይን የሰውን ዐይን ቀለም ቅላት ያመለክታል:: ተገቡ አማራጭ ትርጉሞች እነሆ አት 1)ጥቁር ቀለም ያላቸው ዐይኖች ጤናማ ዐይኖች ናቸው ወይም 2) ብዙ የወይን ጠጅ ከመጠጣት የተነሣ የሰዎች ዐይኖች ይቀላሉ (ተመሣሣይ አባባል እና ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)
ይህ የሰውን ነጭ ጥርስ ከወተት ንጣት ጋር ያነጻጽራል፡፡ ይህም ወተትን የሚጠጡበት ብዙ የሚታለቡ ላሞች እንደሚኖሩ ነው (ተመሣሣይ አባባል እና ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)
ይህ የዛብሎንን ነገድ ያመለክታል:: የዛብሎት ነገድ ወይም ትውልድ በበሕር ዳር ይኖራል (ምትክ ቃላት ይመልከቱ)
እዚህ እርሱ የዛብሎን ሰዎች የሚወርሱት ወይም የሚገነቡት የባሕር ዳር ከተሞችን ይወክላል እነዚህ የወደብ ከተሞች ለመረከበኞች መጠለያ ይሆናሉ (ምትክ ቃል አጠቃቀም ይመልከቱ)
በባህር ዳር ያለ መሬትና ለመርከቦች መቆሚያ ደኀንነት ያለው ቦታ ማለት ነው
ያዕቆብ ስለይሳኮርና ነገድ ወይም ትውልድ ሲናገር እንደ አህያ ይቆጥራቸዋል ይህም እጅግ የሚሠሩ እንደሚሆኑ በአትኩሮት ይገልጻል የይሳኮር ትውልድ አንደ አጥንተ ብርቱ አህያ ነው (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
አብዛኛውን ጊዜ ወደፊት የሚፈጸሙ ትንቢቶች እንደተፈጸመ ተደርጐ ይገለጻል ይህ በአትኩሮት የሚናገረው ክስተቱ በእርግጥ እንደሚፈጸም ነው ይህም በወደፊት ጊዜ ሊገለጽ ይችላል አት “ይሳኮር… ይሆናል” ወይም “የይሳኮር ትውልድ… ይሆናል” (ወደፊት አመላካች ኃላፊ ክስተት ይመልከቱ)
እዚህ ይሳኮር ለነገዱ ምትክ ሆኖ የሚቆም ስም ነው አት “የይሳኮር ትውልዶች… ያያሉ …ይሆናሉ” (ምትክ ቃላት ይጠቀሙ)
ተገቢ ትርጉሞች 1 በጭነት መካከል ይተኛል ወይም 2 በሁለት በጐች አጥር መካከል ይተኛል ደግሞም በሌላ መንገድ ያዕቆብ ስለይሳኮር ልጆች እጅግ እንደሚሠሩና ከዚያም ለእረፍት እንደሚተኙ ይናገራል (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
መልካም እረፍት የሚያገኙበት ቦታና የለማች ምድር
ትከሻውን ለሽክም ያመቻቻል ማለት ሸክምን በመሸከም እጅግ ይሠራል ማለት ነው (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ለሌሎች እንደባሪያ ያገለግላል
እዚህ ዳን ነገዱን ይወክላል የዳን ልጆች በራሱ ሕዝብ ላይ ይፈርዳል ምትክ ቃላት አጠቃቀም ይመልከቱ
ተገቢ ትርጉሞች የራሱ ሕዝብ፤ 1) በዳን ሕዝብ 2) በእስራኤል ሕዝብ
ያዕቆብ ስለዳንና የእርሱ ትውልድ እንደ እባብ አድርጐ ይናገራቸዋል እባብ ምንም ትንሽ ቢሆን መንገደኛውን ከፈረስ ላይ ማውረድ ይችላል እንዲሁ ዳን ትንሽ ነገድ ሲሆን በጠላቶቹ ላይ አደገኛ ነው አት የዳን ልጆች በመንገድ ዳር እንዳለ እባብ ናቸው (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ረቂቅ ስም “ማዳን” እንደ “መዳን” ሊተረጐም ይችላል፡፡ አት “እግዚአብሔር ሆይ እንዲታድነኝ እጠባብቃለሁ”
“እኔ” ያዕቆብን ያመለክታል
ጋድ ትውልዱን ይወክላል:: አት “የጋድ ልጆች ..ይጠቃሉ ነገር ግን እነርሱ” (ምትክ ቃል ይጠቀሙ)
አሴር የአሴር ልጆችን ይወክላል:: እት “የአሴር ልጆች ማእደ ሰፊ… እናም እነርሱ” ምትክ ቃል ይጠቀሙ
ንፍታሌም የንፍታሌምን ትውልድ ይወክላል:: አት “የንፍታሌም ልጆች.. እነርሱ… ይሆናሉ”
ከዳን ልጆች በመሸሽ በተራራማው የሚኖሩ ሰዎችን ያመለክታል
እዚህ የበረከተ የሚለው ምግቡ ጣፋጭ ማለት ነው ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ
ያዕቆብ ስለንፍታሌም ልጆች ለመሮጥ እንደተለቀቀች እንደ እንስት ሚዳቋ እንደሆነ ይናገራል:: ይህም እነርሱ ፈጣን መልእክተኞች እንደሆኑ ነው:: አት “የንፍታሌም ዘሮች እንደተለቀቀች ሚዳቋ ይሆናሉ” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ግልገሎች ትናንሽ የሚዳቋ ግልገሎች ናቸው የዕብራይስጡ ቃል ትርጉም ግልጽ አይደለም አንዳንድ ትርጉሞች መልካም ቃል ይሰጣል ወይም መልካም ነገር ይናገራል የሚለውን ተጠቅመዋል (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ዮሴፍ ትውልዱን/ዘሩን ይወክላል ያዕቆብ እነርሱን ብዙ ፍሬ እንደሚያፈራ የዛፍ ቅርንጫፍ አድርጐ ይናገራል:: አት “የዮሴፍ ዘር ፍሬያማ የዛፍ ቅርንጫፍ ነው”
የዛፍ ዋና ቅርንጫፍ
ቅርንጫፎች አድገው ቅጥርን ማልበሳቸው እነዚያ በቅጥር ላይ እንደሚወጡ ተደርጐ ተገልጾአል (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ያዕቆብ ዮሴፍንና ዘሩን መባረክ ይቀጥላል
ቀስቱን የያዘው ሰው መጽናቱ ቀስቱ ራሱ እንደጸና ተደርጐ ተግልጾአል ወደ ጠላቱ በሚያልምበት ጊዜ ቀስቱ እንደሚጸና ይገልጻል አት ወደ ጠላቱ በሚያልምበት ጊዜ ቀስቱን አጽንቶ ይይዛል (ምትክ ቃላት አጠቃቀም እና ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)
እዚህ “እርሱ” ዘሩን የሚወክለውን ዮሴፍን ነው አት “ቀስቶቻቸውና እጆቻቸው” (ምትክ ቃላት ይመልከቱ)
ቀስትን መያዘ የለመዱ እጆች ስለሆኑ ሙሉ ሰው እንደ እጆች ተገልጾአል:: (ክፍልን እንደሙሉና ሙሉን እንደክፍል የመግልጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
እጆች የእግዚአብሔርን ኃይል ይገልጻሉ:: አት “የሁሉን ቻይ አምላክ ኃይል” (ምትክ ቃላት ይመልከቱ)
እዚህ ስም ሙሉ ሰው ይወክላል አት ከእረኛው የተነሣ (ምትክ ቃላት ይመልከቱ)
ያዕቆብ እግዚአብሔር እረኛ እንደሆነ ይናገራል አት ይህም እግዚአብሔር ሕዝቡን እንደሚመራና እንደሚጠብቅ ይናገራል (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ያዕቆብ እግዚአብሔር ሰዎች የሚወጡበትና ከጠላቶቻቸው የምድኑበት አለት እንደሆነ ይናገራል ይህ የሚያጐላው እግዚአብሔር ሕዝቡን እንደሚጠብቅ ነው (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ያዕቆብ ዮሴፍንና ዘሩን መባረክ ይቀጥላል (ዘፍጥረት 49:22-23 ይመልከቱ)
እዚህ “አንተ” ዘሩን የሚወክለውን ዮሴፍን ያመለክታል አት “የአንተን ዘር በሚረዳ ….በሚባርክህ” (ምትክ ቃላት አጠቃቀም ይመልከቱ)
ሰማይ ተክልን ወይም ሰብልን የሚያሳድገው ዝናብን ይወክላል (ምትክ ቃላት ይመልከቱ)
ጥልቅ ለወንዞችና ለኩሬዎች የሚሆን ውሃ የሚወጣበትን ይወክላል (ምትክ ቃላት ይመልከቱ)
እዚህ ጡቶችና ማህጸን እናቶች የመውለድና ጡት የማጥባት አቅም ያመለክታል (ምትክ ቃላት ይመልከቱ)
ያዕቆብ ዮሴፍንና ልጆቹን መባረክ ይቀጥላል፡፡
የመሠረታዊው ቋንቋ ትርጉም ግልጽ አይደለም:: አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች በጥንት ተራሮች ፈንታ ጥንት አባቶች ይጠቀማሉ::
እዚህ “እነርሱ” የአባቱ በረከቶች ናቸው::
ያዕቆብ እነዚህ በረከቶች ልጆቹ እጅግ በበለጡት ላይ እንዲሆን ይሻል:: አት “እጅግ በበለጡ በዮሴፍ ልጆች ራስ አናት ላይ” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ከወንድሞቹ ዋና በሆነው
ብንያም ዘሩን የሚወክል ምትክ ስም ነው:: ያዕቆብ የብያም ልጆችን እንደ ተራበ ተኩላ ይናገራል:: ይህም አጉልቶ የሚናገረው አጥቂ ተዋጊዎች እንደሆኑ ነው:: የብንያም ነገድ ሰዎች እንደተራቡ ተኩላ ናቸው:: (ምትክ ቃልና ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
እነዚህም በዘፍጥረት 49: 1- 27 የተዘረዘሩትን ይመለከታል እያንዳንዱ ልጅ የነገድ አባት ሆኖአል፡፡
እዚህ “ባረካቸው” የሚለው መደበኛ በረከቶችን እንደተናገረ ነው
ለእያንዳንዱ የሚገባውን በረከት ባረከ
አዘዛቸው
ይህ ለመሞት መድረሱን በትህትና የሚገለጸበት መንገድ ነው፡፡ አት “ለመሞት ቀርበአለሁ ወይም ልሞት ነኝ” (ንኀብነት ወይም ለዛ ባለ መንገድ መግለጽንና ፈሊጣዊ አነጋገርን ይመልከቱ)
ያዕቆብ በሚሞትበት ጊዜ የራሱ ውስጠኛው ሰው/ ነፍሱ ወደየት እንደሚሄድ ያመለክታል:: ከሞት በኋላ አብርሃምንና ይስሐቅን አንደሚገናኝ ይጠብቃል (ንኀብነት ወይም ለዛ ባለ መንገድ መግለጽንና ፈሊጣዊ አነጋገርን ይመልከቱ)
ይህ ወንድ ሰው ስም ነው፡፡ “ኬጢያዊ” የኬጥ ዘር ነው:: በዘፍጥረት 23:8 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ:: (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)
የአንድ ቦታ ወይም ግዛት ስም ነው፡፡ በዘፍጥረት 23፡9 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ፡፡ (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)
ይህ የሔብሮን ከተማ ሌላ ስምዋ ነው:: ምናልባት መምሬ የተባለው የአብርሃም ወዳጅ ስም የተሰየመ ሳይሆን አይቀርም:: በዘፍጥረት 13:18 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ(ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)
ያዕቆብ ለልጆቹ መናገሩን ይቀጥላል
ግዥው ግልጽ ሊደረግ ይችላል:: አት “በዚያ አብርሃም የገዛውን” (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)
ከኬጢያዊያን
“ለልጆቹ መመሪያ መሰጠቱን እንዳበቃ” ወይም “ልጆቹን አዝዞ እንዳበቃ”
ያዕቆብ በአልጋው ላይ ተቀምጦ ነበር አሁን ግን ሊሞት መልሶ እግሮቹን በአልጋ ላይ የሰበስባል
ይህ አንድ ሰው መሞቱን ለዛ ባለ ቋንቋ የሚገለጽበት መንገድ ነው (ንኀብነት ወይም ለዛ ባለ መንገድ መግለጽን ይመልከቱ)
ያዕቆብ በሞተ ጊዜ ውስጠኛው ሰው ወይም ነፍሱ ከእርሱ በፊት የሞቱ ወገኖች ወደሄዱበት ቦታ ተሰብስቦአል (ንኀብነት ወይም ለዛ ባለ መንገድ መግለጽንና ፈሊጣዊ አነጋገርን ይመልከቱ)