Genesis 48

Genesis 48:1

እንዲህም ሆነ

ይህ ሀረግ የታሪኩ አድስ ክፍል መጀመሩን ለማመልከቱ ተጠቅሞአል (አድስ ክስተት ስለማስታወቅ ይመልከቱ)

አንድ ሰው ለዮሴፍ ተናገረው

አደ ሰው ለዮሴፍ ነገረው

እየው፤ አባትህ

ስማ ፤አባትህ፤ እዚህ “እየው” የሚለው ቃል የዮሴፍን ትኩረት ለማግኘት ተጠቅሞአል::

ስለዚህ ይዞ

ስለዚህ ዮሴፍ ይዞ

ለያዕቆብ … በተነገረው ጊዜ

ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል፡፡ አት “አንድ ሰው ለያዕቆብ በነገረው ጊዜ” (ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)

ልጅህ ዮሴፍ ልያይህ ወደ አንተ መጥቶአል

ልጅህ ዮሴፍ መጥቶአል

እስራኤል ተበረታትቶ በአልጋው ላይ ተቀመጠ

እዚህ እስራኤል ተነሥቶ በአልጋው ሊቀመጥ የታገለውን አንድ ሰው አንድን ዕቃ እንደሚሰበስብ ብርታትን እንደሰበሰበ አድርጐ ጸሐፊው ይናገራል:: አት “በአልጋው ተነሥቶ ሊቀመጥ እስራኤል ከፍተኛ ጥረት አድርጐአል ወይም በአልጋው ተነሥቶ ሊቀመጥ እስራኤል ታግሎአል” (ዘይቤያዊ አገላለጽ ይጠቀሙ)

Genesis 48:3

ሎዛ

ይህ የከተማ ስም ነው:: በዘፍጥረት 28:19 የዚህን ከተማ ስም እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)

በከነዓን ምድር … ባረከኝም እንዲህም አለኝ

ይህ በሌላ ሀረግ እንደሚጀምር እንደ አዲስ ዐረፍተ ነገር ሊተረጐም ይችላል:: “በከነዓን ምድር ባረከኝ እናም እንዲህ አለኝ”

ባረከኝ

እግዚአብሔር መደበኛ በረከትን በአንድ ሰው ላይ እንዳደረገ ያመለክታል

እንዲህም አለኝ እነሆ ፍሬያማ አደርግሃለሁ አበዛሃለሁ ለብዙ ሕዝብም ጉባዔ አደርግሃለሁ ይህችንም ምድር ከአንተ በኋላ ለዘላለም ርስት ለዘርህ እሰጣታለሁ

ይህ በጥቅስ ውስጥ ጥቅስን ይዞአል እንደተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊገለጽ ይችላል አት ፍሬያማ እንደሚያደርገኝና እንደሚያበዛች ተናግሮኛል:: እናም ለብዙ ሕዝብም ጉባዔ እንደሚያደርገኝና ይህችንም ምድር ከእኔ በኋላ ለዘላለም ርስት አድርጐ ለዘሬ እንደሚሰጠኝ ነግሮኛል (ጥቅሶችን በጥቅስ ውስጥና ቀጥተኛና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)

እነሆ

እዚህ ቦታ እነሆ የተጠቀመው እግዚአብሔር ሊናገር ስላለው ነገር ያዕቆብ ትኩረት እንዲሰጥ ለማንቃት ነው

ፍሬያማ አደርግሃለሁ አበዛሃለሁ

አበዛሃለሁ የሚለው ሀረግ እግዚአብሔር እንዴት ያዕቆብን ፍሬያማ እንደሚያደርገው ይገልጻል:: አት “ብዙ ዘር/ትውልድ እሰጥሃለሁ” (ድርብ ቃላትና ፈሊጣዊ አነጋገር ይጠቀሙ)

አንተን ለብዙ ሕዝብ ጉባዔ አደርግሃለሁ

እዚህ አንተ ያዕቆብን ቢያመለክትም የያዕቆብን ትውልድ ይወክላል አት “ትውልድህን ብዙ ሕዝቦች አደርጋለሁ” (ምትክ ቃላት ይመልከቱ)

የዘላለም ርስት

ቋሚ ርስት

Genesis 48:5

አሁን

ይህ በዚህን ጊዜ ማለት አይደለም ነገር ግን ለሚቀጥለው ዋና ነጥብ ትኩረት እንዲሰጥበት ተጠቅሞአል

ኤፍሬምና ሚናሴ ለእኔ ናቸው

እንደ ዮሴፍ ወንድሞች ኤፍሬምና ሚናሴ ከምድሪቱ ክፍል የየራሳቸውን ርስት ይቀበላሉ

በርስታቸው በወንድሞቻቸው ስም ይጠራሉ

ተገቢ ትርጉሞች የሚከተሉት ናቸው 1 እንደ ሚናሴና ኤፍሬም ነገዶች ሌሎች የዮሴፍ ልጆች ምድሪቱን ይወርሳሉ 2 ዮሴፍ ከኤፍሬምና ሚናሴ የተለየ ምድር የሰጠዋል እናም የዮሴፍ ሌሎች ልጆች ያን ምድር ይወርሳሉ አት በርስት ድልደላቸው በወንድሞቻቸው ስም ይቆጠራሉ

ኤፍራታ

ይህ የቤተልሔም ከተማ ስም ነው:: በዘፍጥረት 35:16 የዚህን ከተማ ስም እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ::

ያም ቤተልሔም ነው

ጸሐፊው የዳራ መረጃ ይሰጣል (የዳራ መረጃ ይመልከቱ)

Genesis 48:8

እነዚህ እነማን ናቸው?

እነዚህ የማን ወንዶች ልጆች ናቸው?

ባረካቸው

አባት ልጆቹንና የልጅ ልጆቹን እብዛኛውን ጊዜ መደበኛ በረከት ይባርካል

በዚህን ጊዜ የእስራኤል ዐይኖች …. ማየት ተስኖአቸው

በዚህን ጊዜ የሚለው ቃል የተጠቀመው ታሪኩ ወደ እስራኤል ዳራ መረጃ እንደተቀየረ ለማመልከት ነው (ዳራ መረጃ ይመልከቱ)

እርሱም ሳማቸው

እስራኤል ሳማቸው

Genesis 48:11

ፊትህን እንደገና አያለሁ

እዚህ “ፊት” ሙሉ ሰው ይወክላል:: አት እንደገና አይሃለሁ (ክፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን አንደ ክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)

በእስራኤል ጉልበቶች መካከል

ዮሴፍ ልጆቹን በእስራኤል ጭን ወይም ጉልበት ላይ ማስቀመጡ እስራኤል እንደራሱ ልጆች እንደተቀበላው የሚገልጽ ምልክት ነው:: ይህም ለልጆች የወራሽነት መብት ከያዕቆብ ያስገኛል (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)

በግምባሩም ወደ ምድር አጐንብሶ ሰገደ

ዮሴፍ ለአባቱ ክብርን ለመስጠት ወደ ምድር አጐንበሶ ሰገደ (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)

ሚናሴንም በግራው በእስራኤል ቀኝ

እስራኤል ቀኝ እጁን በሚናሴ ላይ እንዲያደርግ ዮሴፍ ልጆቹን ያስቀምጣቸዋል ሚናሴ ታላቅ ወንድም ነው እናም ቀኝ እጅ ትልቅ በረከት የመቀበል ምልክት ነው (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)

Genesis 48:14

ቀኝ እጁን ዘርግቶ በኤፍሬም ራስ ላይ አኖረ

ቀኝ እጁን በኤፍሬም ራስ ላይ ማኖር እርሱ ትልቅ በረከት እንዲቀበል ምልክት ነበር (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)

እስራኤል ዮሴፍን ባረከው

ዮሴፍ ደግሞ ኤፍሬምንና ሚናሴን ይወክላል:: ዮሴፍ አባት ስለሆነ እርሱ ብቻውን ተጠቅሶአል (ክፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን እንደ ክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)

አባቶቼ አብርሃምና ይስሐቅ በፊቱ የሄዱለት እግዚአብሔር

እግዚአብሔርን ማገልገል በእግዚአብሔር ፊት እንደመሄድ ተደርጐ ተነግሮአል አት አያቴ አብርሃምና አባቴ ይስሐቅ ያገለገሉት እግዚአብሔር (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)

እረኛ የሆነኝ

እረኛ በጐቹን እንደምንከባከብ እግዚአብሔር እስራኤልን ተንከባክቦታል አት እረኛ እንስሳትን እንደሚንከባከብ የተንከባከበኝ (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)

መልአክ

ተገቢ ትርጉሞች አት እግዚአብሔር ያዕቆብን ለመጠበቅ የላከውን መልአክ ያመለክታል 2 ይህ እግዚአብሔር ያዕቆብን ለመጠበቅ በመልአክ መልክ የተገለጸውን ያመለክታል

ጠበቀኝ

አዳነኝ

ስሜም የአባቶቼ የአብርሃምና የይስሐቅ ስም በእነርሱ ይጠራ

እዚህ ስም ሰውን ይወክላል ስሜ በእነርሱ ይጠራ የሚለው ሀረግ አንድ ሰው ከሌላ ሰው የተነሣ እንዲታወስ የሚገልጽ ፈሊጣዊ አነጋገር ነው:: ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “ከኤፍሬምና ሚናሴ የተነሣ ሰዎች አብርሃም ይስሐቅንና እኔን ያስታውሱ” (ምትክ ቃል : ፈሊጣዊ አነጋገርና ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)

በምድርም ላይ ይብዙ

እዚህ እነርሱ ኤፍሬምንና ሚናሴን ቢያመለክትም የእነርሱ ትውልድንም ይወክላል:: አት “በምድር ሁሉ ላይ የሚኖር ብዙ ትውልድ ይኑራቸው” (ምትክ ቃል እጠቃቀም ይመልከቱ)

Genesis 48:17

ቀኝ እጅህን እርሱ ራስ ላይ አድርግ

ቀኝ እጅ በኩር ወንድ ልጅ የሚያገኘው ትልቅ በረከት ምልከት ነበር (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)

Genesis 48:19

እርሱ ደግሞ ሕዝብ ይሆናል ታላቅም ይሆናል

እዚህ እርሱ ሚናሴን ቢያመለክትም የእርሱን ትውልድ ይወክላል አት ታላቅ ልጅህ ብዙ ትውልድ ይኖረዋል እናም ታላቅ ሕዝብ ይሆናል (ምትክ ቃላት ይመልከቱ)

በዚያን ቀን በእነዚህ ቃላት

በዚያ ዕለት እንዲህ ብሎ

በእናንተ ስም እስራኤል እንዲህ ብሎ ይባርካል

የእስራኤልም ሰዎች ሌሎችን በሚባርኩበት ጊዜ በስማችሁ ይባርካሉ

በእናንተ ስም እንዲህ ብለው እግዚአብሔር እንደ ኤፍሬምና እንደሚናሴ ያድርጋችሁ

ይህ በጥቅስ ውስጥ ጥቅስን ይዞአል ይህም እንደ ተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊገለጽ ይችላል:: አት “በእናንተ ስም እግዚአብሔር ሌሎችን ሰዎች እንደ ኤፍሬምና እንደ ሚናሴ እንዲያደርግ ይጠይቁታል” (ጥቅሶችን በጥቅስ ውስጥ ቀጥተኛና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)

እንደ ኤፍሬምና እንደ ሚናሴ

እስራኤል ኤፍሬምን አስቀድሞ መጥራቱ ኤፍሬም ከሚናሴ ታላቅ እንደሚሆን የሚገልጽ ነው

እስራኤል ኤፍሬምን ከሚናሴ አስቀድሞታል

ለኤፍሬም ትልቁን በረከት መስጠትና ኤፍሬም ከሚናሴ የተሻለ አድርጐ መውሰድ እስራኤል በአካል ኤፍሬምን ከሚናሴ በፊት እንዳስቀመጠው ተደርጐ ተገልጾአል (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)

Genesis 48:21

ከእናንተ ጋር ይሆናል ወደ አባቶቻችሁም ምድር መልሶ ያገባችኋል

እዚህ “እናንተ” “የእናንተ” ብዙና የእስራኤልን ሕዝብ ሁሉ ያመለክታል (“እናንተ” አጠቃቀም ይመልከቱ)

ከእናንተ ጋር ይሆናል

እግዚአብሔር የእስራኤልን ሕዝብ እንደሚረዳና እንደሚባረካቸው የሚገልጽ ፈሊጣዊ አነጋገር ነው አት እግዚአብሔር ይረዳችኋል ወይም እግዚአብሔር ይባርካችኋል (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)

ወደ አባቶቻችሁም ምድር

ወደ ዘራችሁም ወይም ትውልዳችሁም ምድር

ለአንተ ከወንድሞችህ አንድ እጅ እብልጬ ዐምባ ሰጠሁህ

ተገቢ ትርጉሞች 1 ከወንድሞቹ ይበልጥ ብዙ ክብርና ሥልጣን ለዮሴፍ መሰጠቱ እርሱ በአካል ከሌሎች የበላይ ተደርጐ ተገልጾአል:: አት “ለአንተ ከሌሎች ለሚትበልጠው የተራራውን ዐምባ ሰጠሁህ” ወይም 2)ያዕቆብ ለዮሴፍ ወንድሞች ከሚሰጠው መሬት በላይ ለዮሴፍ እንደሚሰጠው ይገልጻል:: አት “ለአንተ ለወንድሞችህ ከሰጠሁት በላይ ridge ሰጠሁህ የተራራውን ዐምባ ሰጠሁህ” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)

ለአንተ

እዚህ አንተ በነጠላ የተገለጸና ዮሴፍን ያመለክታል (አንተ አጠቃቀም ይመልከቱ)

በሰይፌና በቀስቴ ከአሞራዊያን እጅ የወሰድኳትን ዐምባ

እዚህ ሰይፍ እና ቀስት በጦርነት መዋጋትን ያመለክታሉ፡፡ አት “የተዋጋሁትና ከአሞራዊያን እጅ የወሰድሁት ምድር” (ምትክ ቃላት አጠቃቀም ይመልከቱ)