ይህ ሀረግ የታሪኩ አድስ ክፍል መጀመሩን ለማመልከቱ ተጠቅሞአል (አድስ ክስተት ስለማስታወቅ ይመልከቱ)
አደ ሰው ለዮሴፍ ነገረው
ስማ ፤አባትህ፤ እዚህ “እየው” የሚለው ቃል የዮሴፍን ትኩረት ለማግኘት ተጠቅሞአል::
ስለዚህ ዮሴፍ ይዞ
ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል፡፡ አት “አንድ ሰው ለያዕቆብ በነገረው ጊዜ” (ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)
ልጅህ ዮሴፍ መጥቶአል
እዚህ እስራኤል ተነሥቶ በአልጋው ሊቀመጥ የታገለውን አንድ ሰው አንድን ዕቃ እንደሚሰበስብ ብርታትን እንደሰበሰበ አድርጐ ጸሐፊው ይናገራል:: አት “በአልጋው ተነሥቶ ሊቀመጥ እስራኤል ከፍተኛ ጥረት አድርጐአል ወይም በአልጋው ተነሥቶ ሊቀመጥ እስራኤል ታግሎአል” (ዘይቤያዊ አገላለጽ ይጠቀሙ)
ይህ የከተማ ስም ነው:: በዘፍጥረት 28:19 የዚህን ከተማ ስም እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)
ይህ በሌላ ሀረግ እንደሚጀምር እንደ አዲስ ዐረፍተ ነገር ሊተረጐም ይችላል:: “በከነዓን ምድር ባረከኝ እናም እንዲህ አለኝ”
እግዚአብሔር መደበኛ በረከትን በአንድ ሰው ላይ እንዳደረገ ያመለክታል
ይህ በጥቅስ ውስጥ ጥቅስን ይዞአል እንደተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊገለጽ ይችላል አት ፍሬያማ እንደሚያደርገኝና እንደሚያበዛች ተናግሮኛል:: እናም ለብዙ ሕዝብም ጉባዔ እንደሚያደርገኝና ይህችንም ምድር ከእኔ በኋላ ለዘላለም ርስት አድርጐ ለዘሬ እንደሚሰጠኝ ነግሮኛል (ጥቅሶችን በጥቅስ ውስጥና ቀጥተኛና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)
እዚህ ቦታ እነሆ የተጠቀመው እግዚአብሔር ሊናገር ስላለው ነገር ያዕቆብ ትኩረት እንዲሰጥ ለማንቃት ነው
አበዛሃለሁ የሚለው ሀረግ እግዚአብሔር እንዴት ያዕቆብን ፍሬያማ እንደሚያደርገው ይገልጻል:: አት “ብዙ ዘር/ትውልድ እሰጥሃለሁ” (ድርብ ቃላትና ፈሊጣዊ አነጋገር ይጠቀሙ)
እዚህ አንተ ያዕቆብን ቢያመለክትም የያዕቆብን ትውልድ ይወክላል አት “ትውልድህን ብዙ ሕዝቦች አደርጋለሁ” (ምትክ ቃላት ይመልከቱ)
ቋሚ ርስት
ይህ በዚህን ጊዜ ማለት አይደለም ነገር ግን ለሚቀጥለው ዋና ነጥብ ትኩረት እንዲሰጥበት ተጠቅሞአል
እንደ ዮሴፍ ወንድሞች ኤፍሬምና ሚናሴ ከምድሪቱ ክፍል የየራሳቸውን ርስት ይቀበላሉ
ተገቢ ትርጉሞች የሚከተሉት ናቸው 1 እንደ ሚናሴና ኤፍሬም ነገዶች ሌሎች የዮሴፍ ልጆች ምድሪቱን ይወርሳሉ 2 ዮሴፍ ከኤፍሬምና ሚናሴ የተለየ ምድር የሰጠዋል እናም የዮሴፍ ሌሎች ልጆች ያን ምድር ይወርሳሉ አት በርስት ድልደላቸው በወንድሞቻቸው ስም ይቆጠራሉ
ይህ የቤተልሔም ከተማ ስም ነው:: በዘፍጥረት 35:16 የዚህን ከተማ ስም እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ::
ጸሐፊው የዳራ መረጃ ይሰጣል (የዳራ መረጃ ይመልከቱ)
እነዚህ የማን ወንዶች ልጆች ናቸው?
አባት ልጆቹንና የልጅ ልጆቹን እብዛኛውን ጊዜ መደበኛ በረከት ይባርካል
በዚህን ጊዜ የሚለው ቃል የተጠቀመው ታሪኩ ወደ እስራኤል ዳራ መረጃ እንደተቀየረ ለማመልከት ነው (ዳራ መረጃ ይመልከቱ)
እስራኤል ሳማቸው
እዚህ “ፊት” ሙሉ ሰው ይወክላል:: አት እንደገና አይሃለሁ (ክፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን አንደ ክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
ዮሴፍ ልጆቹን በእስራኤል ጭን ወይም ጉልበት ላይ ማስቀመጡ እስራኤል እንደራሱ ልጆች እንደተቀበላው የሚገልጽ ምልክት ነው:: ይህም ለልጆች የወራሽነት መብት ከያዕቆብ ያስገኛል (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)
ዮሴፍ ለአባቱ ክብርን ለመስጠት ወደ ምድር አጐንበሶ ሰገደ (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)
እስራኤል ቀኝ እጁን በሚናሴ ላይ እንዲያደርግ ዮሴፍ ልጆቹን ያስቀምጣቸዋል ሚናሴ ታላቅ ወንድም ነው እናም ቀኝ እጅ ትልቅ በረከት የመቀበል ምልክት ነው (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)
ቀኝ እጁን በኤፍሬም ራስ ላይ ማኖር እርሱ ትልቅ በረከት እንዲቀበል ምልክት ነበር (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)
ዮሴፍ ደግሞ ኤፍሬምንና ሚናሴን ይወክላል:: ዮሴፍ አባት ስለሆነ እርሱ ብቻውን ተጠቅሶአል (ክፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን እንደ ክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
እግዚአብሔርን ማገልገል በእግዚአብሔር ፊት እንደመሄድ ተደርጐ ተነግሮአል አት አያቴ አብርሃምና አባቴ ይስሐቅ ያገለገሉት እግዚአብሔር (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
እረኛ በጐቹን እንደምንከባከብ እግዚአብሔር እስራኤልን ተንከባክቦታል አት እረኛ እንስሳትን እንደሚንከባከብ የተንከባከበኝ (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)
ተገቢ ትርጉሞች አት እግዚአብሔር ያዕቆብን ለመጠበቅ የላከውን መልአክ ያመለክታል 2 ይህ እግዚአብሔር ያዕቆብን ለመጠበቅ በመልአክ መልክ የተገለጸውን ያመለክታል
አዳነኝ
እዚህ ስም ሰውን ይወክላል ስሜ በእነርሱ ይጠራ የሚለው ሀረግ አንድ ሰው ከሌላ ሰው የተነሣ እንዲታወስ የሚገልጽ ፈሊጣዊ አነጋገር ነው:: ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “ከኤፍሬምና ሚናሴ የተነሣ ሰዎች አብርሃም ይስሐቅንና እኔን ያስታውሱ” (ምትክ ቃል : ፈሊጣዊ አነጋገርና ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)
እዚህ እነርሱ ኤፍሬምንና ሚናሴን ቢያመለክትም የእነርሱ ትውልድንም ይወክላል:: አት “በምድር ሁሉ ላይ የሚኖር ብዙ ትውልድ ይኑራቸው” (ምትክ ቃል እጠቃቀም ይመልከቱ)
ቀኝ እጅ በኩር ወንድ ልጅ የሚያገኘው ትልቅ በረከት ምልከት ነበር (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)
እዚህ እርሱ ሚናሴን ቢያመለክትም የእርሱን ትውልድ ይወክላል አት ታላቅ ልጅህ ብዙ ትውልድ ይኖረዋል እናም ታላቅ ሕዝብ ይሆናል (ምትክ ቃላት ይመልከቱ)
በዚያ ዕለት እንዲህ ብሎ
የእስራኤልም ሰዎች ሌሎችን በሚባርኩበት ጊዜ በስማችሁ ይባርካሉ
ይህ በጥቅስ ውስጥ ጥቅስን ይዞአል ይህም እንደ ተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊገለጽ ይችላል:: አት “በእናንተ ስም እግዚአብሔር ሌሎችን ሰዎች እንደ ኤፍሬምና እንደ ሚናሴ እንዲያደርግ ይጠይቁታል” (ጥቅሶችን በጥቅስ ውስጥ ቀጥተኛና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)
እስራኤል ኤፍሬምን አስቀድሞ መጥራቱ ኤፍሬም ከሚናሴ ታላቅ እንደሚሆን የሚገልጽ ነው
ለኤፍሬም ትልቁን በረከት መስጠትና ኤፍሬም ከሚናሴ የተሻለ አድርጐ መውሰድ እስራኤል በአካል ኤፍሬምን ከሚናሴ በፊት እንዳስቀመጠው ተደርጐ ተገልጾአል (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
እዚህ “እናንተ” “የእናንተ” ብዙና የእስራኤልን ሕዝብ ሁሉ ያመለክታል (“እናንተ” አጠቃቀም ይመልከቱ)
እግዚአብሔር የእስራኤልን ሕዝብ እንደሚረዳና እንደሚባረካቸው የሚገልጽ ፈሊጣዊ አነጋገር ነው አት እግዚአብሔር ይረዳችኋል ወይም እግዚአብሔር ይባርካችኋል (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ወደ ዘራችሁም ወይም ትውልዳችሁም ምድር
ተገቢ ትርጉሞች 1 ከወንድሞቹ ይበልጥ ብዙ ክብርና ሥልጣን ለዮሴፍ መሰጠቱ እርሱ በአካል ከሌሎች የበላይ ተደርጐ ተገልጾአል:: አት “ለአንተ ከሌሎች ለሚትበልጠው የተራራውን ዐምባ ሰጠሁህ” ወይም 2)ያዕቆብ ለዮሴፍ ወንድሞች ከሚሰጠው መሬት በላይ ለዮሴፍ እንደሚሰጠው ይገልጻል:: አት “ለአንተ ለወንድሞችህ ከሰጠሁት በላይ ridge ሰጠሁህ የተራራውን ዐምባ ሰጠሁህ” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
እዚህ አንተ በነጠላ የተገለጸና ዮሴፍን ያመለክታል (አንተ አጠቃቀም ይመልከቱ)
እዚህ ሰይፍ እና ቀስት በጦርነት መዋጋትን ያመለክታሉ፡፡ አት “የተዋጋሁትና ከአሞራዊያን እጅ የወሰድሁት ምድር” (ምትክ ቃላት አጠቃቀም ይመልከቱ)