ይህ በታሪኩ አድስ ክስተት ይጀምራል ይህ በተለይ ከግብዣው ሁለተኛው ቀን ማግሥት የተከሰተውን ያመለክታል፡፡
የቤቱ አዛዥ የዮሴፍ ቤት ተግባራትን ለማስተዳደር ኃላፊነት ያለው ነበር
የእነርሱ ገንዘብ በትንሽ ቦርሳ ውስጥ የተቀመጡ የብር ሳንቲሞች ነበሩ
በስልቻው
የብሩን ዋንጫዬን ጨምረው
ወንድም የሚለው ቃል የታወቀ ነው አት በታናሽ ወንድማቸው ስልቻ (ድብቅ ቃላትን የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
የማለዳ ብርሃን ሲወጣ
ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “ሰዎችን ከነአህዮቻቸው ሸኙአቸው” (ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)
ይህ ጥያቄ ወንድሞቹን ለመቆጣት ተጠቅሞአል:: አት እኛ “ለእናንተ መልካም ካደረግን በኋላ ክፉ መለሳችሁብን” (ሽንገላ አዘል/ rhetorical/ ጥያቄ ይመልከቱ)
ይህ ጥያቄ የተጠቀመው ወንድሞቹን ለመቆጣት ነው፡፡ አት “ይህ ጽዋ ጌታዬ የሚጠጣበትና የተሰወረ ነገርንም የሚያውቅበት እንደሆነ በእርግጥ ታውቃችሁ” (ሽንገላን የያዘ ጥያቄ ይመልከቱ) ይህ ያደረጋችሁት የፈጸማችሁት ድርጊት ክፉ ነው ያደረጋችሁት የሚለውን መደጋገሙ ትኩረት ለመስጠት ነው አት የፈጸማችሁት ነገር እጅግ ክፉ ነው ተመሣሣይ ተጓዳኝ ንጽጽር ነው::
ዮሴፍ የነገራቸው የነገረውን ነገራቸው
“ቃል” የተናገረውን ነገር:: ይወክላል ወንድሞቹ የቤቱን አዛዥ እንደ “ጌታዬ” ያመለክታሉ:: ይህ በከፍተኛ ኃላፊነት ላሌ ሰው የሚነገር መደበኛ አባባል ነው:: አት “ጌታዬ ለምን እንደዚህ ይናገራሉ?” (ምትክ ቃላት አጠቃቀም ዘይቤና አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)
አንድ ሰው አንድን ነገር የማያደርገው ያ ሰው አንድን ዕቃ ከራሱ አርቆ እንደማስቀመጥ ተደርጐ ተገልጾአል፣ (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
“እኛ ስለምንናገረው ነገር ያድምጡ እናም የምንናገረው ነገር እውነት እንደሆነ ያያሉ፤ ብሩ”
“በየስልቾቻችን ያገኘነውን ብር ያውቃሉ”
ከከነዓን መልሰን ወደ አንተ አምጥተናል
ወንድምቹ ከግብጽ ጌታ እንዳልሠረቁ እትኩሮት ለመስጠት ጥያቄ ይጠቀማሉ:: አት “ስለዚህ ከጌታህ ቤት የወሰድነው ምንም ነገር የለም!” (ሽንገላ አዘል ጥያቄዎችን ይመልከቱ)
እንዚህ በጣምራ ቃላት የተጠቀሙት ዋጋ ያለውን ምንም ነገር እንዳልሠረቁ ለመግለጽ ነው
ወንድምች ራሳቸውን እንደ “የአንተ አገልጋዮች” ይገልጻሉ:: ይህ ከፍተኛ ስልጣን ላለ ሰው የሚነገር መደበኛ መንገድ ነው:: እንዲሁም ይህ የተገኘበት ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክሊገለጽ ይችላል:: አት “ከእኛ አንዱ ጽዋውን/ዋንጫውን የሠረቀ ከተገኘ” (አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ሰው አገለላለጽና ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)
እዚህ ጌታችን የቤቱን አዛዥ ያመለክታል ይህ በሁለተኛ ሰው መልክ ሲገለጽ ይችላል አት እንደባሪዎች ሊትወስደን ትችላለህ (አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ሰው አገለላለጽ ይመልከቱ)
መልካም ነው: እንዳላችሁት አደርጋለሁ:: እዚህ “አሁን” “በዚህ ጊዜ” ማለት አይደለም ነገር ግን የሚቀጥለው ዋና ነጥብ ትኩረትን ለመሳብ ተጠቅሞአል::
ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል አት ከስልቾቻችን በአንዱ ጽዋውን ካገኘው ያ የተገኘበት ሰው ባሪያዬ ይሆናል (ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)
የየራሱን ስልቻ አራገፌ
“ወንድም” የተባለው ቃል የታወቀ ነው:: “ከታላቅ ወንድም ….እስከ ታናሽ ወንድም” (የተደበቁ ቃላትን የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
ይህ እንደ አድስ ዐረፍተ ነገርና ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊተረጐም ይችላል በታናሹ ወንድም የቤቱ አዛዥ ጽዋውን በብንያምን ስልቻ አገኘ (ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)
እዚህ እነርሱ ወንድምቹን ያመለክታል ልብስን መቅደድ የታላቅ ሐዘን ወይም ተካዜ ምልክት ነው (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)
በየአህዮቻቸው…. እናም ተመለሱ
ዮሴፍ እዚያው ነበረ
በፊቱም መሬት ላይ ወደቁ:: ይህ ወንድምቹ ጌታው ምሕረት እንዲያደርግላቸው የመፈለጋቸው ምልክት ነው:: (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)
ዮሴፍ ወንድሞቹን ለመቆጣት ጥያቄ ይጠቀማል:: አት “እንደ እኔ ያለ ሰው ስውር ነገርን በጥበብ እንደሚያውቅ ታውቃላችሁ” (ሽንገላን ያዘለ ጥያቄ ይመልከቱ)
ሶስቱም ጥያቄዎች ሁሉ ተመሣሣይ ትርጉም አላቸው:: የተደረገውን ለመግለጽ የሚናገሩት ምንም እንደሌለ ትኩረት ለመስጠት እነዚህን ጥያቄዎች ይጠቀማሉ፡፡ አት “ጌታዬ የምንናገረው የለንም የሚረባ ነገር መናገር አንችልም ራሳችንን ንጹህ ማድረግ አንችልም” (ተመሣሣይ ተጓዳኝ አገላለጽ እና ሽንገላ አዘል ጥያቄዎች ይመልከቱ)
እዚህ ጌታዬ ዮሴፍን ያመለክታል ይህ ለአንድ ከፍተኛ ባለሥልጣን የሚነገርለት መደበኛ መንገድ ነው በሁለተኛ ወገን ሰው መንገድ ሊገለጽ ይችላል:: አት “ምን አንላለን … ባሪያዎችህ” (አንደኛ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)
ወንድሞቹ ራሳቸውን እንደ ባሪያዎች ያቀርባሉ :: እዚህ ገለጠ የሚለው እግዚአብሔር ወንድሞቹ ያደረጉትን ገለጠ ማለት አይደለም:: ነገር ግን እነርሱ ስላደረጉት ነገር እግዚአብሔር እየቀጣቸው ነው የሚል ትርጉም አለው:: አት “እግዚአብሔር ላለፈው ኃጢአት እየቀጣቸው ነው”
ወንድሞቹ ራሳቸውን እንደ ባሪያዎች ያቀርባሉ:; ይህ ለአንድ ከፍተኛ ባለሥልጣን የሚነገርለት መደበኛ መንገድ ነው:: በአንደኛ ወገን ሰው መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “በደላችንን” (አንደኛ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)
እዚህ “እጅ” ሙሉ ሰው ይወክላል:: እንዲሁም የተገኘበት የሚለው ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል:; አት “ጽዋህን የወሰደው” (ምትክ ቃል አጠቃቀምና ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)
አንድ ሰው የማያደርገው አንድ ነገር ያ ሰው ከራሱ አርቆ የሚያቀምጠው ዕቃ ተደርጐ ተገልጾአል:: አት “ያን ነገር የሚያደርግ የእኔ ዓይነት አይደለም” (ዘይቤያዊ አነጋYገር ይመልከቱ)
እዚህ “እጅ” ሙሉ ሰው ይወክላል:: እንዲሁም የተገኘበት የሚለው ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል:; አት “ጽዋዬን የወሰደው ሰው” (ምትክ ቃል አጠቃቀምና ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)
ተጠግቶ
ይሁዳ ራሱን እንደ “አገልጋይህ ወይም ባሪያህ” ያመለክታል:: ይህ ለአንድ ከፍተኛ ባለሥልጣን የሚነገርለት መደበኛ መንገድ ነው:: ይህ በአንደኛ ወገን ሰው መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “እኔ ባሪያህ ወይም አገልጋይህ”(አንደኛ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)
“ጆሮ” የሚለው ለሙሉ ሰው የሚሆን ምትክ ቃል ነው፡፡ አት “ጌታዬ ሊናገርህ” (ምትክ ቃል አጠቃቀም ይመልከቱ)
እዚህ ጌታዬ ዮሴፍን ያመለክታል፡፡ ይህ ለአንድ ከፍተኛ ባለሥልጣን የሚነገርለት መደበኛ መንገድ ነው:: ይህ በሁለተኛ ወገን ሰው መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “ለአንተ”(አንደኛ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)
መቆጣት እንደሚያቃጥል እሳት ተደርጐ ተገልጾአል:: አት “አባክህን እኔን አገልጋይህን አትቆጣኝ” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ጌታው ትልቅ ሥልጣን እንዳለው ትኩረት ለመስጠት ከፈርዖን ጋር ያወዳድረዋል:: ይህም የሚገልጸው ሊቆጣውም ሊገድለውም እንደሚችል ነው አት “እንደ ፈርዖን ኃይለኛ ስለሆንህና ወታደሮችህም ሊገድሉኝ ስለሚችሉ” (ግምታዊ እውቀትና ጥልቀ መረጃ ይመልከቱ)
ይህ በጥቅስ ውስጥ ጥቅስ የያዘ ነው እንደ ተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊገለጽ ይችላል:: አት “ጌታዬ አባት ወይም ወንድም እንዳለን ጠየቀን” (ጥቅስን በጥቅስ ውሰጥ እና ቀጥታና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)
ይሁዳ ዮሴፍን “ጌታዬ” እና “እርሱ” በሚሉ ቃላት ያመለክተዋል:: አንዲሁም ደግሞ ወንድሞቹንና ራሱን እንደ “የእርሱ ባሪያዎች” ይገልጻል:: አት “አንተ ጌታዬ ባሪያዎችህን ጠየቅሄን ወይም አንተ ጠቀየቅሄን” (አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ወገን አገላለጽ ይመልከቱ)
በዮሴፍ ፊት መናገሩን ይሁዳ ቀጠለ
ይህ በጥቅስ ውስጥ ጥቅስ የያዘ ነው እንደ ተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊገለጽ ይችላል:: አት “እናም እኛ እንዲህ አልን ‘አባት አለን አባቱም ይወድደዋል’” (ጥቅስን በጥቅስ ውሰጥ እና ቀጥታና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)
ይሁዳ ዮሴፍን እንደ “ጌታዬ” ያመለክተዋል:: ይህ ለአንድ ከፍተኛ ባለሥልጣን የሚነገርለት መደበኛ መንገድ ነው:: አት “ጌታዬ እኛም እንዲህ አልን”(አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ወገን አገላለጽ ይመልከቱ)
ይህ ለጓደኛ ወዳጅ ወይም ለቤተሰብ አባል ያለውን ፍቅር ይገልጻል
ይህ በጥቅስ ውስጥ ጥቅስ የያዘ ነው እንደ ተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊገለጽ ይችላል:: አት “እናም አንተ ለባሪያዎችህን ታናሽ ወንድማችሁን አምጡት እኔም አየዋለሁ አልህ’” (ጥቅስን በጥቅስ ውሰጥ እና ቀጥታና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)
ይሁዳ ወንድሞቹንና ራሱን እንደ እርሱ ባሪያዎች ያመለክታል:: አት “ከዚያም ለእኛ ለባሪያዎችህ እንዲህ አልህ”(አንደኛ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ወገን አገላለጽ ይመልከቱ)
ከከነዓን ወደ ግብጽ መጓዝ ሲነገር መውረድ የሚለው ቃል የተለመደ ነው:: አት “ወደ እኔ አምጡት” (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)
ይህ በጥቅስ ውስጥ ጥቅስ የያዘ ነው እንደ ተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊገለጽ ይችላል:: አት “መልሰን እኛም ለጌታዬ ልጁ ….አይችልም፤ ….አባትየው ይሞታል” (ጥቅስን በጥቅስ ውሰጥ እና ቀጥታና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)
ከማዘን የተነሣ አባታቸው እንደሚሞት ይገልጻል (ግምታዊ እውቀት ወይም ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)
ይሁዳ ታሪኩን ለዮሴፍ መናገር ቀጠለ
ይህ በጥቅስ ውስጥ ጥቅስ የያዘ ነው እንደ ተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊገለጽ ይችላል:: አት “ከዚያም ለባሪያዎችህ ታናሽ ወንድማችን ከእኛ ጋር ካልመጣ ፊቴን አታዩም አልሄን ” (ጥቅስን በጥቅስ ውሰጥ እና ቀጥታና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)
ይሁዳ ራሱንና ወንድሞቹን እንደ “እርሱ ባሪያዎች” ያመለክታል፡፡ ይህ ትልቅ ባለሥልጣን ለሆነ ለአንድ ሰው የሚነገርለት መደበኛ መንገድ ነው፡፡ (አንደኛ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ወገን አገላለጽ ይመልከቱ)
ከከነዓን ወደ ግብጽ መጓዝ ሲነገር መውረድ የሚለው ቃል የተለመደ ነው::
እዚህ “ፊት” ሙሉ ሰውን ይወክላል:: አት እንደገና አታዩኝም (ምትክ ቃላት አጠቃቀም ይመልከቱ)
ይህ ሀረግ የተጠቀመው የታሪኩ አድስ ክፍል መጀመሩን ለማመለከት ነው:: በቋንቋዎ ይህን የሚገልጹበት መንገድ ካለ ይጠቀሙ:: (አድስ ክስተት ስለማስታወቅ ይመልከቱ)
ከግብጽ ወደ ከነዓን መጓዝ ሲነገር “ወደ ላይ መውጣት” የሚለውን ሀረግ መጠቀም የተለመደ ነው
ይሁዳ ዮሴፍን እንደ “ጌታዬ” ያመለክታል:: አት ጌታዬ የነገርከውን ቃል ነገርነው”(አንደኛ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ወገን አገላለጽ ይመልከቱ)
ይህ በጥቅስ ውስጥ ጥቅስ የያዘ ነው እንደ ተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊገለጽ ይችላል:: አት “አባታችን አንደገና ወደ ግብጽ በመሄድ ለእኛና ለቤተሰቦቻችን እህል እንድንሸምት ተናገረን ” (ጥቅስን በጥቅስ ውሰጥ እና ቀጥታና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)
ይህ በጥቅስ ውስጥ ጥቅስ የያዘ ነው እንደ ተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊገለጽ ይችላል:: አት “ከዚያም ለእርሱ ወደ ግብጽ መውረድ አንችልም አልን ታናሽ ወንድማችን ከእኛ ጋር … ከእኛ ጋር ” (ጥቅስን በጥቅስ ውሰጥ እና ቀጥታና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)
እዚህ ፊት ሙሉ ሰውን ይወክላል:: አት “ሰውየውን ለማየት” (ምትክ ቃላት አጠቃቀም ይመልከቱ)
እንዲህ አለን ሚስቴ ሁለት ወንዶች ልጆችን እንደወለደችልን እናንተ ታውቃላችሁ አንዱ ከእኔ ወጣ አውሬ በላው አላችሁኝ እስከ ዛሬም አላየሁትም ይህንም ከእኔ ለይታችሁ ደግሞ ብትወስዱ ክፉም ቢያገኘው ሽበቴን በሐዘን ወደ መቃበር ታወርዱታላችሁ ይህ ሁለት ደረጃና ሶስት ደረጃ ጥቅሶችን ይዞአል እነዚህም እንደተዘዋዋሪ ጥቅሶች ሊገለጹ ይችላሉ አት እንዲህ አለን ሚስቱ ራሔል ሁለት ወንዶች ልጆችን ብቻ እንደወለደችለት እናውቃለን ከእነርሱ አንዱ ወጣና አውሬ በላው እናም እስከ ዛሬ አላየሁትም ሌላውን ልጅ ብንወስደውና ክፉ ቢያገኘው በሐዘን እንዲሞት እናደርጋለን (ጥቅስን በጥቅስ ውሰጥ እና ቀጥታና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)ከዚይ አለ
እዚህ “እኛ” ዮሴፍን አያካትትም (ነጠላና ብዙ ወይም አካታች “እኛ” ይመልከቱ)
እዚህ “እናንተ” ብዙና ወንድሞቹን ያመለክታል (“እናንተ” አጠቃቀም ዓይነት ይመልከቱ)
ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል አት አውሬ በላው ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ
ለአንድ ሰው አንድ ክፉ ነገር የሚደርሰበት ጉዳት ወደዚያ ሰው እንደሚመጣ ተደርጐ ተቆጥሮአል (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
“ወደ መቃብር ማውረድ” እንዲሞትና ወደ መቃብር እንዲወርድ ማድረግ ማለት ነው:: “ማውረድ” የሚለውን ቃል የተጠቀመው መቃብር በመሬት ውስጥ እንደሆነ በተለምዶ የታወቀ ስለሆነ ነው:: አት “ከዚያም እኔን ሽማግሌውን በሐዘን እንዲሞት ታደርጋላችሁ” (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ያዕቆብን የሚያመለክትና ሽምግልናውን አበክሮ የሚናገር ነው:: አት “እኔ ሽማግለው” (ምትክ ቃል አጠቃቀም ይመልከቱ)
ይህ በዚህን ጊዜ ማለት አይደለም ነገር ግን ለሚቀጥለው ጠቃሚ ነገር ትኩረት እንዲሰጥበት ተጠቅሞአል
ይሁዳ ያለ ብንያምን ወደ አባቱ በሚመለስበት ጊዜ ምን ሊፈጠር እንደሚችል የሚገምተውን ነገር ግን እውነት የሆነውን ለዮሴፍ ይገልጻል (ግምታዊ ሁኔታዎችን ይመልከቱ)
እዚህ “መምጣት” “መሄድ” ወይም “መመለስ” በሚለው መተርጐም ይችላል::
ልጁ ከእኛ ጋር አለመኖር
አባታቸው ልጁ ከሞቴ እሞታለሁ ያለው አባባል የሁለቱ ሕይወት በአካል በጥብቅ የተሣሠረ እንደሆነ ተደርጐ ተገልጾአል:: አት “እርሱም ልጁ ካልተመለሰ እሞታለሁ ስላለ” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ይሁዳ ወደፊት ይሆናል ብሎ ስለሚገምተው ነገር በእርግጥ እደሚደረግ አድርጐ ይናገራል (ግምታዊ ሁኔታዎች ይመልከቱ)
ወደ መቃብር ማውረድ እንዲሞትና ወደ መቃብር እንዲወርድ ማድረግ ማለት ነው:: “ማውረድ” የሚለውን ቃል የተጠቀመው መቃብር በመሬት ውስጥ እንደሆነ በተለምዶ የታወቀ ስለሆነ ነው:: አት “እናም ሽማግሌውን አባታችንን በሐዘን እንዲሞት እናደርጋለን” (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ይሁዳ ራሱንና ወንድሞችን “ባሪያዎችህ” ብሎ ያመለክታል:: ይህ ለአንድ ትልቅ ባለሥልጣን መደበኛ መንገድ የሚነገርለት ነው:: አት “እኛ አገልጋዮችህ” ወይም “እናም እኛ” (አንደኛ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ወገንነ ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)
እዚህ “ሽበት” ያዕቆብን የሚወክልና ሽምግልናውን የሚናገር ነው:: አት “ሽማግሌው አባታችን” (ምትክ ቃላት አጠቃቀም ይመልከቱ) ስለ ልጁ ደኀንነት በአባቴ ፊት ራሴን ዋስ አድርጌአለሁ ረቂቅ ስም ዋስ ተስፋ በሚለው ግሥ ሊገለጽ ይችላል አት ልጁን በሚመለከት ለአባቴ ተስፋ ስጥቼዋለሁ ረቂቅ ስሞች ይመልከቱ
ይሁዳ ራሱን “ባሪያህ” ብሎ ያመለክታል፡፡ አት “ለእኔ ለባሪያህ” ወይም “ለእኔ” (አንደኛ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)
እንደበደለኛ መቆጠር በደል እንድሰው የሚሸከመው ነገር ተደርጐ ተገልጾአል:: አት “አባቴ ይወቅሰኛል” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ይህ በአሁን ጊዜ ማለት አይደለም ነገር ግን ለሚቀጥለው ዋና ነጥብ ትኩረት እንዲሰጥበት ተጠቅሞአል::
ይሁዳ ራሱን “ባሪያህ” ብሎ ያመለክታል፡፡ አት “እኔ ለባሪያህ” ወይም “እኔ” (አንደኛ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)
ከግብጽ ወደ ከነዓን መጓዝ በሚነገርበት ጊዜ መውጣት የሚለውን ሀረግ መጠቀም የተለመደ ነበር
ብንያምን ወደ ቤት ካልተመለሰ አባቱ ሊኖረው የሚችለውን ሐዘን ለማተኮር ይሁዳ ጥያቄ ይጠቀማል:: አት “ልጁ ከእኔ ጋር ካልሆነ ወደ አባቴ መመለስ እልችልም“ (አግናኝ ወይም ሽንገላ አዘል ጥያቄዎች ይመልከቱ)
ከባድ መከራ የደረሰበት ሰው በዚያው ሰው ክፉ ነገር እንደመጣበት ተደርጐ ተነግሮአል (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)