ከነዓን የሚለው ቃል የታወቀ ነው ይህ ሃሳብ ግልጽ ሊደረግ ይችላል አት በከነዓን ምድር ራቡ የጸና ነበር (ድብቅ ቃላትን የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
ይህ ሀረግ የተጠቀመው የታሪኩን አድስ ክፍል መጀመሩን ለማመልከት ነው በቋንቋዎ ይህን መግለጽ የሚችሉበት መንገድ ካለ ይጠቀሙ (አድስ ክስተት ስለማስታወቅ ይመልከቱ)
ያዕቆብና ቤተሰቡ በልተው ከጨረሱ በኋላ
የያዕቆብ ታላቅ ልጆች ያመጡትን
እዚህ እኛ ያዕቆብን የያዕቆብን ልጆችና የቀሩ የቤተሰብ አባላትን ያመለክታል:: (ሁሉን አካታች “እኛ” ይመልከቱ)
ይሁዳ ለአባቱ ለያዕቆብ እንዲህ አለው
ይህ ዮሴፍን ነው የሚያመለክተው ነገር ግን ወንድምቹ ዮሴፍ መሆኑን አላወቁትም ነበር:: እነርሱም እርሱን ያመለከቱን እንደ “ያ ሰው” ወይም በዘፍጥረት 42:3ዐ እንደተነገረው “ያ ሰው የምድሪቱ ጌታ” ነው::
ይህ በጥቅስ ውስጥ ጥቅስ ይዞአል ይህም እንደ ተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊገለጽ ይችላል:: አት “ታናሽ ወንድማችንን ይዘነው ካላመጣን ፊቱን ማየት እንደማንችል አስጠንቅቆናል” (ጥቅሶችን በጥቅስ ውስጥና ቀጥታና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)
እንዲህም በማለት በጥብቅ አስጠንቀቆናል
ወደ ግብጽ አገር ያለ ብንያም መመለስ እንደማይችሉ ለአባቱ ለማጽናት በዘፍጥረት 43፡ 4-5 ይሁዳ ይህን ሀረግ ሁለት ጊዜ ይጠቀማል:: ፊቴን የሚለው የዚያ ሰው የዮሴፍ ፊት ያመለክታል:: አት “ፊቴን አታዩም” (ክፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን እንደ ክፍል የመግለጽ ዜይቤ ይጠቀሙ)
ይሁዳ ራሔል ከመሞትዋ በፊት የወለደችውን የመጨረሻ ልጅ ብንያምን ያመለክታል
ከከነዓን ወደ ግብጽ ጉዞ በሚነገርበት ጊዜ “ወደታች መውረድ” የሚለውን ሀረግ መጠቀም የተለመደ ነው
ለምን ይህ ችግር እንዲደርስብኝ አደረጋችሁ?
ሰውየው ብዙ ጥያቄዎችን ጠየቀን
እዚህ እኛ የሚለው በተለይ የሚያመለክተው ወደ ግብጽ የወረዱና ከሰውየው ጋር የተነጋገሩ ወንድሞችን ነው
ይህ በጥቅስ ውስጥ ጥቅስን ይዞአል እንደ ተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊጠቀስ ይችላል አት አባታችን በሕይወት እንዳለና ሌላ ወንድም እንዳለን በቀጥታ ጠይቆናል:: (በጥቅሶችን በጥቅስ ውስጥና ቀጥታና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)
የጠየቀንን ጥያቄዎች መለስንለት
ሰውየው ምን ማድረግ እንዳለባቸው እንደሚነግር ልጆቹ አለማወቃቸውን አጽንተው ለመንገር ጥያቄ ይጠቀማሉ ይህ አግናኝ ጥያቄ በዐረፍተ ነገር መልክ ሊተረጐም ይችላል አት እንደዚህ … እንደሚለን አላወቅንም ነበር (አግናኝ ጥያቄዎችን ይመልከቱ)
ይህ በጥቅስ ውስጥ ጥቅስን ይዞአል እንደተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊገለጽ ይችላል አት ወንድማችንን የዘን ወደ ግብጽ እንድንወርድ እንደሚነግረን (በጥቅሶችን በጥቅስ ውስጥና ቀጥታና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)
ከከነዓን ወደ ግብጽ ጉዞ በሚነገርበት ጊዜ “ወደታች መውረድ” የሚለውን ሀረግ መጠቀም የተለመደ ነው
እንድንድን እና እንዳንሞት የሚሉ ሀረጐች ተመሣሣይ ትርጉም አላቸው:: ይሁዳም በሕይወት ለመኖር ከግብጽ አህል መሸመት እንዳለባቸው በማጽናት ይናገራል:: አት “መላው ቤተሰባችን እንዲተርፍ ወደ ግብጽ ወርደን እህል መሸመት ይገባናል” (ተመሣሣይ ተጓዳኝ ንጽጽር ይመልከቱ)
እዚህ እኛ ወደ ግብጽ የሚጓዙ ወንድሞችን ያመለክታል:: (የሚያቅፍና የማያቅፍ እኛ ይመልከቱ)
እዚህ “እኛ” ወንድሞች እስራኤልና መላውን ቤተሰብ ያመለክታል (የሚያቅ “እኛ” ይመልከቱ)
እዚህ እኛ ወንድማማቾችን ያመለክታል (የሚያቅፍና የማያቅፍ “እኛ” ይመልከቱ)
እዚህ አንተ በነጠላ የተገለጸና እስራኤልን ያመለክታል (ሁለተኛ ወገን ሰው ወይም አንተ አጠቃቀም ይመልከቱ)
እኛ ወንድሞችን ያመለክታል በረሀቡ ጊዜ ሊሞቱ የሚችሉ ትናንሽ ልጆችን ያመለክታል
“ዋስ” የተባለው ረቂቅ ስም እንደ “ተስፋ” የተባለው ግሥ ሊገለጽ ይችላል፡፡ (ረቂቅ ስሞች ይመልከቱ)
ያዕቆብ ይሁዳን እንዴት ተጠያቂ እንደሚያደረገው በግልጽ መነገር አለበት አት በብንያም ላይ በሚደርሰው ነገር ሁሉ ምላሽ እንዲሰጥ ታደርገኛለህ (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይጠቀሙ)
ይህ አንድ ሰው እንደሚሸከመው ዕቃ ተደርጐ ኃላፊነትን መሸከም ይገልጻል (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ይሁዳ ቀድሞ መደረግ የነበረበት ነገር ግን ያልተደረገውን ነገር ይገጻል ተጨማሪ እህል ለመሸመት ልጆቹ ወደግብጽ ሳይሄዱ በመቆየታቸው አባቱን እንስራኤልን ይሁዳ በመውቀስ ይናገረዋል (የሚገመቱ ታሳቢ ሁኔታዎችን ይመልከቱ)
ሁለት ጊዜ መመላለስ በቻልን
ይህ ብቸኛ ምርጫችን ከሆነ ይህን አድረጉ
ከከነዓን ወደ ግብጽ መጓዝ በሚነገርበት ጊዜ መውረድ የሚለውን ቃል መጠቀም የተለመደ ነበር
ቆዳን ለማከምና ለመከላከል የሚጠቀሙበት ጣፊጨነት ያለው ቅባታማ ፍሬ ነው:: በዘፍጥረት 37:25 ይህን ቃል እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ:: አት “መድኃኒት”
የተለያዩ ቅመማ ቅመሞች በዘፍጥረት 37:25 እነዚህን ቃላት እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ
ትናንሽ አረንጓዴ ተክል ለውዞች (ያልታወቁትን ስለመተርጐም ይመልከቱ)
ጣፋጭ ጣዕም ያለው የዛፍ ፍሬ (ያልታወቁትን ስለመተርጐም ይመልከቱ)
እዚህ “እጅ” ሙሉ ሰውን ይወክላል አት ዕጥፍ ገንዘብ ውሰዱ (ክፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን እንደክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
እዚህ እጅ ሙሉ ሰውን ይወክላል በስልቼቻችሁ አፍ የተመለሰው ብር የተባለው ሀረግ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “አንድ ሰው በስልቾቻችሁ የጨመረውን ብር መልሳችሁ ወደ ግብጽ ውሰዱ” (ክፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን እንደ ክፍል የመግለጽ ዘይቤና ተሻጋሪ ግሥና የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)
ብንያምንም ደግሞ ውሰዱ
ተመለሱ
ምሕረት የሚለው ረቂቅ ስም ርኀራኄ በሚለው ቅጽል ሊተረጐም ይችላል:: አት “ሁሉን የሚችል አምላክ ያ ሰው እንዲራራ ያድርግላችሁ” (ረቂቅ ስሞች ይመልከቱ)
ስምዖንን
ልጆቼን ካጣሁ ያው አጣሁ ያዕቆብ ልጆቹን ቢያጣ እንዳጣ ሊቀበል አውቆታል ማለት ነው
እዚህ “እጅ” ሙሉ ሰውን ይወክላል:: አት እነርሱም … ወሰዱ (ክፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን እንደክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
ከከነዓን ወደ ግብጽ መጓዝ በሚነገርበት ጊዜ “ወደዚያ ወረደ” የሚለውን ሀረግ መጠቀም የተለመደ ነበር
ብንያም ከዮሴፍ ታላቅ ወንድሞች ጋር
የቤቱ አዛዥ የዮሴፍን ቤት ተግባራትን ለማሰተዳደር ኃላፊነት ነበረው
እዚህ “አመጣቸው” እንደ “ወሰዳቸው” ሊተረጐም ይችላል:: (“መጣ” እና “ሄደ” አጠቃቀም ይመልከቱ)
ወደ ዮሴፍ ቤት ውስጥ
የዮሴፍ ወንድሞች ፈሩ
ይህ ተሻጋሪ ግስ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል፡፤ አት “ወደ ዮሴፍ ቤት ይሄዱ ነበር” ወይም “የቤቱ አዛዥ ወደ ዮሴፍ ቤት ይወስዳቸው ነበር” (ተሻጋሪና የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)፡፡
ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል አት የቤቱ አዛዥ እየወሰደን ያለው ያነ አንድ ሰው በስልቾቻችን በጨመረው ብር ሰበብ ነው (ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)
ይህ እንደ አድስ ዐረፍተ ነገር ሊተረጐም ይችላል:: አት “ሊከሰን እጋጣሚ እየጠበቀ ስላለ ሊያሰረን ይሆናል”
ወንድሞቹ ለቤቱ አዛዥ መናገር ቀጠሉ
ይህ ሀረገ በታሪኩ ዋና ክተት ለማመልከት ተጠቅሞአል በቋንቋዎ ይህን የሚገልጹበት መንገድ ካለ ይጠቀሙ::
ለአዳር በሠፈርንበት ቦታ በደረስን ጊዜ
እዚህ “እነሆ” የሚለው ቃል ወንድሞቹ ባዩት ነገር እንደተገረሙ ለማሳየት ተጠቅሞአል::
እያንዳንዳችን በየስልቾቻችን ሙሉውን ብሮቻችንን አገኘው
እዚህ እጆች ሙሉውን ሰው ይወክላሉ አት ብሮቻችንን መልሰን የዘነው መጣን (ክፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን እንደክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
እዚህ እጆች ሙሉ ሰው ይወክላሉ:: አት “ደግሞም እህል መሸመቻ የሚሆነንን ብር ይዘን መጥተናል” (ክፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን እንደክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
ከከነዓን ወደ ግብጽ መጓዝ በሚነገርበት ጊዜ “ወደዚያ ወረደ” የሚለውን ሀረግ መጠቀም የተለመደ ነበር
ረቂቅ ስም ሰላም እንደ ግሥ ሊገለጽ ይችላል:: አት “ዘና በሉ ወይም ተረጋጉ” (ረቂቅ ስሞችን ይመልከቱ)
የቤቱ አዛዥ ሁለት የተለያዩ አምላኮችን እየተናገረ አይደለም አት “አምላካችሁ አባታችሁ የሚያመለከው”
ይህ ባህል ረጅም ጉዞ ተጉዘው ከመጡ በኋላ የደከሙ መንገደኞች ድካማቸው እንዲቀል የሚረዱበት ነው:: የዚህ ዐረፍተ ነገር ሙሉ ትርጉም ግልጽ ሊደረግ ይችላል:: (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልክቱ)
ገፈራ ለከበቶች የሚሆን ድርቆሽ ነው
“እጅ” ሙሉን ሰው ይወክላል:: አት “ወንድሞች ያመጡአቸውን እጅ መንሻቸውን” (ክፍልን እንደሙሉና ሙሉን እንደ ክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
ይህ ክብርና አክብሮት የሚገለጽበት መንገድ ነው:: (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)
አባታቸውን እንደ “አገልጋይህ” ማመልከታቸው አክብሮታቸውን ለማሳየት ነው አት “አባታችን የሚያገለግልህ”
እነዚህ ቃላት በመሠረቱ ተመሣሣይ ትርጉም አላቸው በሰውየው ፊት ጐንበስ በማለት አክብሮታቸውን ገለጹ:: አት “በፊቱ ሰገዱለት” (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)
ቀና ብሎ ሲመለከት ማለት ነው ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ
ይህ በአድስ ዐረፍተ ነገር መልክ ሊተረጐም ይችላል:: አት “የእናቱን ልጅ.. አየ:: ዮሴፍም አለ፤”
ተገቢ አማራጭ ትርጉሞች 1 ይህ ሰው ብንያምን እንደሆነ ለማረጋገጥ ዮሴፍ በውኑ ይጠይቃቸዋል ወይም 2) ይህ አግናኝ ጥያቄ ነው:: “ደግሞ ይህ ታናሽ ወንድማችሁ …. “ (አግናኝ ጥያቄዎችን ይመልከቱ)
ይህ አንድ ሰው በዝቅተኛ ደረጃ ላለ ሌላ ሰው በጓደኝነት መንገድ የሚጠራው አጠራር ነው:: አት “ወጣቱ”
ተቻኩሎ ከክፍሉ ወጣ
ስሜቱ በጥልቀት የሚለው ሀረግ አንድ መልካም ነገር ሲከሰት የሚሰማ ታላቅ ስሜትን ያመለክታል:: አት “ለወንድሙ የመራራት ጠንካራ ስሜት ነበረው” ወይም “ለወንድሙ ጠንካራ የናፍቆት ስሜት ነበረው” (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ዮሴፍ እንደሚናገር ግልጽ ማድረግ ይቻላል:: አት “እናም ለአገልጋዮቹ አላቸው” (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)
ሰዎች እንዲመገቡ ምግብን ማቅረብ ማለት ነው፡፡
ይህም ዮሴፍ ወንድሞቹና ሌሎች በአንድ ክፍል በተለያየ ቦታ ተቀምጠው ይመገባሉ ማለት ነው አገልጋዮችም ለዮሴፍ ለብቻው ለመንድሞቹም ለብቻቸው እናም ከእርሱ ጋር ለሚበሉ ግብጻዊያን ደግሞ ለብቻቸው አቀረቡላቸው
እነዚህ ምናልባት ከእርሱ ጋር የሚበሉ የግብጽ ባለሥልጣናት ይሆናሉ ነገር ግን ከዮሴፍና ከዕብራዊያን ወንድሞቹ ተለይተው ተቀምጠዋል
ይህ እንደ አዲስ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል ይህንን ያደረጉበት ምክንያት ግብጻዊያን ከዕብራዊያን ጋር መመገብ ጸያፍ አድርገው ያስባሉ
እዚህ እንጀራ ጠቅላላ ምግብ ይወክላል (ክፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን እንደ ክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
እያንዳንዱ ወንድም የት መቀመጥ እንዳለበት ዮሴፍ እንዳዘጋጀ ሊገመት ይገልጻል የተገለጸውን መረጃ ግልጽ ማድረግ ይቻላል አት የሚቀመጡበት ቦታ በተዘጋጀላቸው መሠረት በሰውየው/ዮሴፍ ፊት ወንድሞቹ ተቀመጡ (ግምታዊ እውቀት ወይም ጥልቅ መረጃ ይጠቀሙ)
“በኩር”ና “ታናሽ” የተጠቀሙት ሁሉም ወንድሞች በአንድነት እንደየዕድሜያቸው በተርታ እንደተቀመጡ ለመግለጽ ነው::( ነጠላ ነገር በብዙ የመግለጽ ዘይቤ/merism/ ይመልከቱ)
ይህን ባወቁ ጊዜ ሰዎቹ በጣም ተገረሙ
አምስት እጥፍ የሚለው ሀረግ በአጠቃላይ ብዙ በሚለው ሊገለጽ ይችላል:: አት “ብንያም የተቀበለው ድርሻ ወንድሞቹ ከተቀበሉት በጣም ብዙ ነበር”