Genesis 7

Genesis 7:1

ወደ መርከቡ የሚገቡት ሰባት ወንድና ሴት እንስሶች የትኞቹ ነበሩ?

ንጹሕ ከሆኑት እንስሳት ሰባት ወንድና ሴት እንዲሁም ወፎች ወደ መርከቡ መግባት ነበረባቸው

Genesis 7:4

እግዚአብሔር ዝናቡ በምድር ላይ ሳያቋርጥ የሚዘንበው ለምን ያህል ጊዜ ነው አለ?

እግዚአብሔር ዝናቡ ለአርባ ቀንና ሌሊት ሳያቋርጥ እንደሚዘንብ ተናገረ

Genesis 7:6

የጥፋት ውሃ በምድር ላይ በመጣ ጊዜ የኖኅ ዕድሜ ምን ያህል ነበር?

የጥፋት ውሃ በምድር ላይ በመጣ ጊዜ የኖኅ ዕድሜ ስድስት መቶ አመት ነበር

Genesis 7:8

ኖኅ እንስሶቹን ወደ መርከቡ ያመጣቸው እንዴት አድርጎ ነበር?

እንስሳቱ ወደ ኖኅ መጡና ወደ መርከቡ ገቡ

Genesis 7:11

የጥፋት ውሃ የመጣው ከየትኞቹ ሁለት መነሻዎች ነበር?

ውሃው የመጣው ከምድር ጥልቅና ከሰማይ ነበር

Genesis 7:15

ሰዎቹ ሁሉና እንስሳቱ ወደ መርከቡ ከገቡ በኋላ በሩን ማን ዘጋው?

እግዚአብሔር አምላክ በሩን ከበስተኋላቸው ዘጋው

Genesis 7:19

ውሃው ከምድር ምን ያህል ከፍታ ነበረው?

ውሃው ከተራራዎቹ ጫፍ በላይ አሥራ አምስት ክንድ ያህል ተነሣ

Genesis 7:21

በጥፋት ውሃው ምክንያት በምድር ላይ የሞተው ምንድነው?

በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱ ፍጥረታት ሁሉና ሰዎች ሁሉ ሞቱ

Genesis 7:23

በምድር ላይ በሕይወት የቀሩት ብቸኞች ሰዎች እነማን ነበሩ?

ኖኅና ከእርሱ ጋር በመርከቡ ውስጥ የነበሩት ብቻ በሕይወት ተረፉ