UDB ክስተቶች በቅደም ተከተል ሲያስቀምጥ ULB ጸሐፊው እንዳስቀመጠ ይዘረዝራል (የክስተቶች ቅደም ተከተል ይመልከቱ)
ባሪያዎችህ በጎችን እናረባለን
የዮሴፍ ወንድምች ራሳቸውን እንደ “ባሪያዎችህ” ያቀርቡታል:: ይህ ብዙ ኃላፊነት ላለው ሰው የሚነገርለት መደበኛ መንገድ ነው:: ይህም እንደ አንደኛ ወገን ሰው ሊገለጽ ይችላል:: አት “እኛ ባሪያዎችህ ወይም እኛ” (አንደኛ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)
“እኛና ቅድመ አባቶቻችን ሁላችን” ወይም “እኛና አባቶቻችን ሁሉ”
በግብጽ ለጊዜው ለመኖር መጥተናል
በጎች የሚሠሩበት ሣር የለምና
ይህ በዚህን ጊዜ ማለት አይደለም ነገር ግን ለሚቀጥለው ዋና ነገር ትኩረት ለመስጠት ነው::
“የግብጽ ምድር ለአንተ ክፍት ነው” ወይም “መላው የግብጽ ምድር በአንተ እጅ ነው”
አባትህንና ወንድሞችህን ምርጥ በሆነው በጌሤም ምድር አኑራቸው
ይህ የሚገለጸው ከብት የማርባት ችሎታ እንዳላቸው ነው:: አት “ከመካከላቸው ከብት በማርባት ትልቅ ችሎታ ያላቸውን የሚቃውቅ ከሆነ” (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)
እዚህ “ባረከው” የሚለው ለዚያ ሰው አዎንታዊና ጠቃሚ ነገሮች እንዲሆኑለት መሻቱን ገለጸ ማለት ነው
እድሜህ ስንት ዓመት ነው?
የእንግድነቴ ዘመን የሚለው ሀረግ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ በመዘዋወር በምድር ላይ ምን ያህል እንደኖረ ያመለክታል:: አት “በምድር ላይ በእንግድነት ያሳለፍኩት ዘመን 13ዐ ዓመት ነው” (ቁጥሮችን ይመልከቱ)
ከአብርሃምና ከይስሐቅ የሕይወት ዘመን ጋር ስነጻጸር ዮሴፍ የሕይወቱ ዘመን አጭር እንደሆነ ይናገራል
ያዕቆብ በሕይወቱ ብዙ ሥቃይና ችግር ተለማምዶአል
ከዚያም ዮሴፍ አባቱንና ወንድሙን ተንከባከባቸው በሚኖሩበት ሥፍራ እንዲመሠረቱ አደረገ
ይህ የጐሼም ምድር ሌላው ስም ነው (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)
እዚህ “ልጆች” በቤተሰብ ጥገኝነት ያሉ ትናንሽ ልጆች ማለት ነው:: አት “በየቤተሰቡ በሚገኙ ትናንሽ ልጆች ቁጥር”
ይህ ቃል ዋናው ታሪክ በመሃል የሚቋረጥበትን ለማመልከት ተጠቅሞአል:: በዚህ ጸሐፊው የታሪኩን አድስ ክፍለ መናገር ይጀምራል::
ይህ በእነዚህ አገሮች የሚኖሩ ሰዎችን ያመለክታል አት የግብጽ ሰዎችና የከነዓን ሰዎች (ምትክ ቃላት ይመልከቱ)
ተቀጨ ወይም ደከመ
ዮሴፍም የግብጽና የከነዓን ሰዎች ገንዘባቸውን ሁሉ ከዮሴፍ እህል ለመሸመት አውለዋል
ገንዘቡን እንዲሰበስቡና እንዲያመጡ ዮሴፍ አገልጋዮቹን እንዳዘዘ ይገመታል (ምትክ ቃላት ይመልከቱ)
እዚህ ምድር በዚያ ምድር የሚኖሩ ሰዎችን ይወክላል:: ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊተረጐም ይችላል:: አት “የግብጽና የከነዓን ሕዝቦችም ገንዘባቸው ባለቀ ጊዜ” (ምትከ ቃላት አጠቃቀምና ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)
ከግብጽ ምድር እና ከከነዓን ምድር
ሰዎች እህል ለመሸመት እንዴት እንደጓጉ ትኩረት ለመሰጠት ጥቃቄ ይጠቀማሉ፡፡ ይህ ጥያቄ በዐረፍተ ነገር መልክ ሊተረጐም ይችላል፡ አት “ገንዘባችን ስላለቀብን እባካችሁ እንድንሞት አታድርጉ!” (ሽንገላ አዘል አግናኝ ጥያቄዎችን ይመልከቱ)
እህል ምግብን በአጠቃላይ ይወክላል:: አት “እህልን ሰጣቸው” ወይም “እህልን አደላቸው” (ክፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን እንደ ክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
ሰዎች ወደ ዮሴፍ መጡ
ሰዎችን ዮሴፍን እንደ” ጌታችን” ያመለክታሉ ይህ ትልቅ ሥልጣን ላሌው ሰው የሚነገርለት መደበኛ መንገድ ነው:: ይህ እንደ ሁለተኛ ወገን ሰው ሊገለጽ ይችላል:: አት” ከጌታችን የምንሰውረው የለም” ወይም “ከአንተ የምንሰውረው የለም” (አንደኛ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)
እዚህ ፊት ዮሴፍን ያመለክታል:: አት “ለጌታችን የምንሰጠው የቀረ የለንም” (ምትክ ቃላት ይመልከቱ)
እዚህ ዐይኖች የዮሴፍን እይታ ያመለክታሉ ሰዎች እህልን ለመግዛት ምንኛ እንደጓጉ ለማተኮር ጥያቄ ይጠቀማሉ ይህ ጥያቄ እንደ ዐረፍተ ነገር ሊተረጐም ይችላል:: አት “እኛ ስንሞት ምድራችም ስትጐዳ እባክህን እንዲሁ ዝም ብለህ አትመለከተን” (ምትክ ቃላት አጠቃቀምና ሽንገላ አዘል አግናኝ ጥያቄዎችን ይጠቀሙ)
የተዘራበት ዘር ስለሌለባት ምድሪቱ የተጐዳችና ጥቅም የሌላት መሆንዋ ምድሪቱ እንደሚትሞት ተደርጐ ተነግሮአል (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ስለዚህ ምድሪቱ የፈርዖን ሆነች
ነገር ግን የካህናቱን መሬት አልገዛም
ድርጐ በቋሚነት አንድ ሰው ለሌላ ሰው የሚሰጠው የገንዘብ ወይም የመግብ መጠን ነው:: ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “ፈርዖን በየዕለቱ ለካህናት የተወሰነ ምግብ ይሰጥ ነበር” (ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)
ፈርዖን ከሰጣቸው ይመገቡ ነበር
ሊትዘሩ ትችላላችሁ
አምስት እጅ የሚለው ቃል ክፍልፋይ ነው፡፡ አት “በመከር ጊዜ እህላችሁን በአምስት መደብ ትከፍላላችሁ አንዱን መደብ እንደክፍያ ለፈርዖን ትሰጡታላችሁ እናም አራቱ መደቦች ለእናንተ ይሆናሉ” (ክፍልፋዮችን ይመልከቱ) ለቤተሰቦቻችሁና ለልጆቻችሁ ምግብ ታደርጉታላችሁ (የተደበቁትን ስለመግልጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
ሞገስ ማግኘት የሚለው ሀረግ በአንድ ሰው ተቀባይነትን ማግኘት የሚገልጽ ፈሊጣዊ አነጋገር ነው:: ደግሞም ዐይኖች ማየትንና ማየት ሃሳብንና በየናን ይወክላል:: አት “በእኛ ከተደሰትክ” (ፈሊጣዊና ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
“በግብጸ ምድር ላይ” ወይም “በመላው የግብጽ ምድር”
ጸሐፊው እስከጻፈበት ጊዜ ድረስ
በዘፍጥረት 47:24 አንድ እምስተኛ እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ
በዙ የሚለው ቃል እንዴት እንደአፈሩ ይገልጻል እነርሱም ብዙ ልጆች ነበሩአቸው (ድርብ ቃላት ይመልከቱ)
እዚህ ፍሬያማ መበልጸግ ወይም ብዙ ልጆች መኖር ማለት ነው
17 ዓመታት (ቁጥሮችን ይመልከቱ)
ያዕቆብ የኖረው 147 ዓመት ነው (ቁጥሮችን ይመልከቱ)
ይህ ጊዜ እንደሚጓዝና አንድ ቦታ እንደሚመጣ ይናገራል:: አት “እስራኤል የሚሞትበት ጊዜ እንደደረሰ” (ዘይቤያዊ አገላለጽ ይመልከቱ)
እዚህ ዓይኖች የማየት ምትክ ቃል ነው እናም ማየት ሃሳብን ወይም አመለካከትን ይወክላል:: አት “በአንተ ፊት ሞገስ ካገኘሁ ወይም ካስደሰትኩህ” (ምትክ ቃላትና ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ይህ በዚህን ጊዜ ማለት አይደለም ለሚቀጥለው ጠቃሚ ነጥብ ትኩረት እንዲሰጥበት ነው
አንድ ሰው በአንድ ሰው ተቀባይነቱን ማረጋገጥ ማለት ነው ፈሊጣሊ አነጋገር ይመልከቱ
ለጠንቃቃ ቃል መግባት የሚደረግ ምልክት ነው በዘፍጥረት 24:2 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)
በጐነት እና ታማኝነት የተባሉ ረቂቅ ስሞች እንደ ቅጽል ስሞች ሊተረጐሙ ይችላሉ አት በበጐነትና በታማኝነት አድርግልኝ ረቂቅ ስሞች ይመልከቱ
እባክህን የሚለው ለዚህ ጥያቄ እጽንዖት ይሰጣል
ማንቀላፋት መሞትን ለዘብ ባለ ቃል የሚገልጽ ነውፀፀ አት “በሚሞትበትና ከዚህ ቀደም የሞቱ ቤተሰቦቼን በሚገናኝበት ጊዜ” (ንኀብነት ወይም ለዘብ ባለና በተዘዋዋሪ መንገድ አንድን ነገር የመግልጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
“ተስፋ ስጠኝ” ወይም “ማልልኝ”
“ተስፋ ሰጠው” ወይም “ቃል ገባለት”