Genesis 44

Genesis 44:1

አጠቃላይ መረጃ

ይህ በታሪኩ አድስ ክስተት ይጀምራል ይህ በተለይ ከግብዣው ሁለተኛው ቀን ማግሥት የተከሰተውን ያመለክታል፡፡

የቤቱ አዛዥ

የቤቱ አዛዥ የዮሴፍ ቤት ተግባራትን ለማስተዳደር ኃላፊነት ያለው ነበር

የሁሉም ሰው ገንዘብ

የእነርሱ ገንዘብ በትንሽ ቦርሳ ውስጥ የተቀመጡ የብር ሳንቲሞች ነበሩ

በስልቻው አፍ

በስልቻው

ዋንጫየን የብሩን ዋንጫዬን… ጨምረው

የብሩን ዋንጫዬን ጨምረው

በታናሹ ወንድማቸው ስልቻ አፍ

ወንድም የሚለው ቃል የታወቀ ነው አት በታናሽ ወንድማቸው ስልቻ (ድብቅ ቃላትን የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)

Genesis 44:3

ጎህ ሲቀድ

የማለዳ ብርሃን ሲወጣ

ሰዎቹ ከነአህዮቻቸው ተሸኙ

ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “ሰዎችን ከነአህዮቻቸው ሸኙአቸው” (ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)

ለበጎ ነገር ስለምን ክፉ መለሳችሁ?

ይህ ጥያቄ ወንድሞቹን ለመቆጣት ተጠቅሞአል:: አት እኛ “ለእናንተ መልካም ካደረግን በኋላ ክፉ መለሳችሁብን” (ሽንገላ አዘል/ rhetorical/ ጥያቄ ይመልከቱ)

ይህ ጌታዬ የሚጠጣበት የተሰወረ ነገርም የሚያውቅበት ጽዋ አይደለምን?

ይህ ጥያቄ የተጠቀመው ወንድሞቹን ለመቆጣት ነው፡፡ አት “ይህ ጽዋ ጌታዬ የሚጠጣበትና የተሰወረ ነገርንም የሚያውቅበት እንደሆነ በእርግጥ ታውቃችሁ” (ሽንገላን የያዘ ጥያቄ ይመልከቱ) ይህ ያደረጋችሁት የፈጸማችሁት ድርጊት ክፉ ነው ያደረጋችሁት የሚለውን መደጋገሙ ትኩረት ለመስጠት ነው አት የፈጸማችሁት ነገር እጅግ ክፉ ነው ተመሣሣይ ተጓዳኝ ንጽጽር ነው::

Genesis 44:6

ይህንም ቃል ነገራቸው

ዮሴፍ የነገራቸው የነገረውን ነገራቸው

ጌታዬ እንደዚህ ያለውን ቃል ለምን ይናገራል?

“ቃል” የተናገረውን ነገር:: ይወክላል ወንድሞቹ የቤቱን አዛዥ እንደ “ጌታዬ” ያመለክታሉ:: ይህ በከፍተኛ ኃላፊነት ላሌ ሰው የሚነገር መደበኛ አባባል ነው:: አት “ጌታዬ ለምን እንደዚህ ይናገራሉ?” (ምትክ ቃላት አጠቃቀም ዘይቤና አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)

ይህን ነገር ማድረግ ከባሪያዎችህ ይራቅ

አንድ ሰው አንድን ነገር የማያደርገው ያ ሰው አንድን ዕቃ ከራሱ አርቆ እንደማስቀመጥ ተደርጐ ተገልጾአል፣ (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)

Genesis 44:8

እነሆ…ብር

“እኛ ስለምንናገረው ነገር ያድምጡ እናም የምንናገረው ነገር እውነት እንደሆነ ያያሉ፤ ብሩ”

በየስልቾቻችን አፍ የተገኘውን ብር

“በየስልቾቻችን ያገኘነውን ብር ያውቃሉ”

ከከነዓን አገር መልሰን ወደ አንተ አምጥተናል

ከከነዓን መልሰን ወደ አንተ አምጥተናል

ታዲያ ብር ወይም ወርቅ ከጌታህ ቤት እንዴት እንሰርቃለን?

ወንድምቹ ከግብጽ ጌታ እንዳልሠረቁ እትኩሮት ለመስጠት ጥያቄ ይጠቀማሉ:: አት “ስለዚህ ከጌታህ ቤት የወሰድነው ምንም ነገር የለም!” (ሽንገላ አዘል ጥያቄዎችን ይመልከቱ)

ብር ወይም ወርቅ

እንዚህ በጣምራ ቃላት የተጠቀሙት ዋጋ ያለውን ምንም ነገር እንዳልሠረቁ ለመግለጽ ነው

ከአገልጋዮችህ ይህ የተገኘበት

ወንድምች ራሳቸውን እንደ “የአንተ አገልጋዮች” ይገልጻሉ:: ይህ ከፍተኛ ስልጣን ላለ ሰው የሚነገር መደበኛ መንገድ ነው:: እንዲሁም ይህ የተገኘበት ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክሊገለጽ ይችላል:: አት “ከእኛ አንዱ ጽዋውን/ዋንጫውን የሠረቀ ከተገኘ” (አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ሰው አገለላለጽና ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)

እኛ ደግሞ የጌታችን ባሮች እንሁን

እዚህ ጌታችን የቤቱን አዛዥ ያመለክታል ይህ በሁለተኛ ሰው መልክ ሲገለጽ ይችላል አት እንደባሪዎች ሊትወስደን ትችላለህ (አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ሰው አገለላለጽ ይመልከቱ)

አሁን እንዲሁ እንደነገራችሁ ይሁን

መልካም ነው: እንዳላችሁት አደርጋለሁ:: እዚህ “አሁን” “በዚህ ጊዜ” ማለት አይደለም ነገር ግን የሚቀጥለው ዋና ነጥብ ትኩረትን ለመሳብ ተጠቅሞአል::

ጽዋው የተገኘበት ባሪያዬ ይሆናል

ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል አት ከስልቾቻችን በአንዱ ጽዋውን ካገኘው ያ የተገኘበት ሰው ባሪያዬ ይሆናል (ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)

Genesis 44:11

የየራሱን ስልቻ ወደ ምድር አወረደ

የየራሱን ስልቻ አራገፌ

ከታላቁ … እስከታናሹ

“ወንድም” የተባለው ቃል የታወቀ ነው:: “ከታላቅ ወንድም ….እስከ ታናሽ ወንድም” (የተደበቁ ቃላትን የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)

ጽዋው በታናሹ በብንያም ስልቻ ተገኘ

ይህ እንደ አድስ ዐረፍተ ነገርና ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊተረጐም ይችላል በታናሹ ወንድም የቤቱ አዛዥ ጽዋውን በብንያምን ስልቻ አገኘ (ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)

በዚህን ጊዜ እነርሱ ልብሳቸውን ቀደዱ

እዚህ እነርሱ ወንድምቹን ያመለክታል ልብስን መቅደድ የታላቅ ሐዘን ወይም ተካዜ ምልክት ነው (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)

በየአህዮቻቸው…ተመለሱ

በየአህዮቻቸው…. እናም ተመለሱ

Genesis 44:14

እርሱ ገና እዚያው ነበረ

ዮሴፍ እዚያው ነበረ

በፊቱም መሬት ላይ ተደፉ

በፊቱም መሬት ላይ ወደቁ:: ይህ ወንድምቹ ጌታው ምሕረት እንዲያደርግላቸው የመፈለጋቸው ምልክት ነው:: (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)

እንደ እኔ ያለ ሰው ምሥጢርን እንዲያውቅ አታውቁምን

ዮሴፍ ወንድሞቹን ለመቆጣት ጥያቄ ይጠቀማል:: አት “እንደ እኔ ያለ ሰው ስውር ነገርን በጥበብ እንደሚያውቅ ታውቃላችሁ” (ሽንገላን ያዘለ ጥያቄ ይመልከቱ)

Genesis 44:16

ለጌታዬ ምን እንመልሳለን? ምንስ እንናገራለን? ወይም በመን እንነጻለን?

ሶስቱም ጥያቄዎች ሁሉ ተመሣሣይ ትርጉም አላቸው:: የተደረገውን ለመግለጽ የሚናገሩት ምንም እንደሌለ ትኩረት ለመስጠት እነዚህን ጥያቄዎች ይጠቀማሉ፡፡ አት “ጌታዬ የምንናገረው የለንም የሚረባ ነገር መናገር አንችልም ራሳችንን ንጹህ ማድረግ አንችልም” (ተመሣሣይ ተጓዳኝ አገላለጽ እና ሽንገላ አዘል ጥያቄዎች ይመልከቱ)

ለጌታዬ ምን እንላለን …. የጌታዬ ባሪያዎች

እዚህ ጌታዬ ዮሴፍን ያመለክታል ይህ ለአንድ ከፍተኛ ባለሥልጣን የሚነገርለት መደበኛ መንገድ ነው በሁለተኛ ወገን ሰው መንገድ ሊገለጽ ይችላል:: አት “ምን አንላለን … ባሪያዎችህ” (አንደኛ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)

እግዚአብሔር የአገልጋዮችን/የባሪያችህን በደል ገልጦአል

ወንድሞቹ ራሳቸውን እንደ ባሪያዎች ያቀርባሉ :: እዚህ ገለጠ የሚለው እግዚአብሔር ወንድሞቹ ያደረጉትን ገለጠ ማለት አይደለም:: ነገር ግን እነርሱ ስላደረጉት ነገር እግዚአብሔር እየቀጣቸው ነው የሚል ትርጉም አለው:: አት “እግዚአብሔር ላለፈው ኃጢአት እየቀጣቸው ነው”

የባሪያዎችህን በደል

ወንድሞቹ ራሳቸውን እንደ ባሪያዎች ያቀርባሉ:; ይህ ለአንድ ከፍተኛ ባለሥልጣን የሚነገርለት መደበኛ መንገድ ነው:: በአንደኛ ወገን ሰው መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “በደላችንን” (አንደኛ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)

እንግዲህ ጽዋው በእጁ የተገኘበት

እዚህ “እጅ” ሙሉ ሰው ይወክላል:: እንዲሁም የተገኘበት የሚለው ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል:; አት “ጽዋህን የወሰደው” (ምትክ ቃል አጠቃቀምና ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)

ይህን ማድረግ ከእኔ ይራቅ

አንድ ሰው የማያደርገው አንድ ነገር ያ ሰው ከራሱ አርቆ የሚያቀምጠው ዕቃ ተደርጐ ተገልጾአል:: አት “ያን ነገር የሚያደርግ የእኔ ዓይነት አይደለም” (ዘይቤያዊ አነጋYገር ይመልከቱ)

ጽዋው በእጁ የተገኘበት ሰው

እዚህ “እጅ” ሙሉ ሰው ይወክላል:: እንዲሁም የተገኘበት የሚለው ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል:; አት “ጽዋዬን የወሰደው ሰው” (ምትክ ቃል አጠቃቀምና ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)

Genesis 44:18

ቀረብ ብሎ

ተጠግቶ

እኔ አገልጋይህ

ይሁዳ ራሱን እንደ “አገልጋይህ ወይም ባሪያህ” ያመለክታል:: ይህ ለአንድ ከፍተኛ ባለሥልጣን የሚነገርለት መደበኛ መንገድ ነው:: ይህ በአንደኛ ወገን ሰው መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “እኔ ባሪያህ ወይም አገልጋይህ”(አንደኛ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)

በጌታዬ ጆሮ አንዲት ቃል እንድናገር

“ጆሮ” የሚለው ለሙሉ ሰው የሚሆን ምትክ ቃል ነው፡፡ አት “ጌታዬ ሊናገርህ” (ምትክ ቃል አጠቃቀም ይመልከቱ)

በጌታዬ ጆሮ

እዚህ ጌታዬ ዮሴፍን ያመለክታል፡፡ ይህ ለአንድ ከፍተኛ ባለሥልጣን የሚነገርለት መደበኛ መንገድ ነው:: ይህ በሁለተኛ ወገን ሰው መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “ለአንተ”(አንደኛ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)

እኔን አገልጋይህን ቁጣህ አያቃጥለኝ

መቆጣት እንደሚያቃጥል እሳት ተደርጐ ተገልጾአል:: አት “አባክህን እኔን አገልጋይህን አትቆጣኝ” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)

አንተ እንደፈርዖን ነህና

ጌታው ትልቅ ሥልጣን እንዳለው ትኩረት ለመስጠት ከፈርዖን ጋር ያወዳድረዋል:: ይህም የሚገልጸው ሊቆጣውም ሊገድለውም እንደሚችል ነው አት “እንደ ፈርዖን ኃይለኛ ስለሆንህና ወታደሮችህም ሊገድሉኝ ስለሚችሉ” (ግምታዊ እውቀትና ጥልቀ መረጃ ይመልከቱ)

ጌታዬ ባሪያዎቹን፤ “አባት አላችሁ ወይም ወንድም?”ብሎ ጠየቀ::

ይህ በጥቅስ ውስጥ ጥቅስ የያዘ ነው እንደ ተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊገለጽ ይችላል:: አት “ጌታዬ አባት ወይም ወንድም እንዳለን ጠየቀን” (ጥቅስን በጥቅስ ውሰጥ እና ቀጥታና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)

ጌታዬ ባሪያዎቹን ጠየቀ

ይሁዳ ዮሴፍን “ጌታዬ” እና “እርሱ” በሚሉ ቃላት ያመለክተዋል:: አንዲሁም ደግሞ ወንድሞቹንና ራሱን እንደ “የእርሱ ባሪያዎች” ይገልጻል:: አት “አንተ ጌታዬ ባሪያዎችህን ጠየቅሄን ወይም አንተ ጠቀየቅሄን” (አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ወገን አገላለጽ ይመልከቱ)

Genesis 44:20

አጠቃላይ መረጃ

በዮሴፍ ፊት መናገሩን ይሁዳ ቀጠለ

እኛም ለጌታዬ እንዲህ አልን ‘ሽማግሌ አባት አለን …. አባቱም ይወድደዋል’

ይህ በጥቅስ ውስጥ ጥቅስ የያዘ ነው እንደ ተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊገለጽ ይችላል:: አት “እናም እኛ እንዲህ አልን ‘አባት አለን አባቱም ይወድደዋል’” (ጥቅስን በጥቅስ ውሰጥ እና ቀጥታና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)

ለጌታዬ እንዲህ አልን

ይሁዳ ዮሴፍን እንደ “ጌታዬ” ያመለክተዋል:: ይህ ለአንድ ከፍተኛ ባለሥልጣን የሚነገርለት መደበኛ መንገድ ነው:: አት “ጌታዬ እኛም እንዲህ አልን”(አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ወገን አገላለጽ ይመልከቱ)

አባቱም ይወድደዋል

ይህ ለጓደኛ ወዳጅ ወይም ለቤተሰብ አባል ያለውን ፍቅር ይገልጻል

ከዚያም ለባሪያዎችህ ወደእኔ አምጡት እኔም አየዋለሁ እልህ

ይህ በጥቅስ ውስጥ ጥቅስ የያዘ ነው እንደ ተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊገለጽ ይችላል:: አት “እናም አንተ ለባሪያዎችህን ታናሽ ወንድማችሁን አምጡት እኔም አየዋለሁ አልህ’” (ጥቅስን በጥቅስ ውሰጥ እና ቀጥታና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)

ከዚያም ለባሪያዎችህ እንዲህ አልህ

ይሁዳ ወንድሞቹንና ራሱን እንደ እርሱ ባሪያዎች ያመለክታል:: አት “ከዚያም ለእኛ ለባሪያዎችህ እንዲህ አልህ”(አንደኛ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ወገን አገላለጽ ይመልከቱ)

ወደ እኔ ይዛችሁ ውረዱ

ከከነዓን ወደ ግብጽ መጓዝ ሲነገር መውረድ የሚለው ቃል የተለመደ ነው:: አት “ወደ እኔ አምጡት” (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)

ከዚያም በኋላ ጌታዬን አልነው “ብላቴናው… አይሆንለትም …አባቱ ይሞታልና”

ይህ በጥቅስ ውስጥ ጥቅስ የያዘ ነው እንደ ተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊገለጽ ይችላል:: አት “መልሰን እኛም ለጌታዬ ልጁ ….አይችልም፤ ….አባትየው ይሞታል” (ጥቅስን በጥቅስ ውሰጥ እና ቀጥታና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)

አባትዬው ይሞታል

ከማዘን የተነሣ አባታቸው እንደሚሞት ይገልጻል (ግምታዊ እውቀት ወይም ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)

Genesis 44:23

አጠቃላይ መረጃ

ይሁዳ ታሪኩን ለዮሴፍ መናገር ቀጠለ

ከዚያም ባሪያዎችህን እንዲህ አልሄን፤ ታናሽ ወንድማችሁ ከእናንተ ጋር ጋር ካልመጣ ዳግመኛ ፊቴን አታዩም

ይህ በጥቅስ ውስጥ ጥቅስ የያዘ ነው እንደ ተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊገለጽ ይችላል:: አት “ከዚያም ለባሪያዎችህ ታናሽ ወንድማችን ከእኛ ጋር ካልመጣ ፊቴን አታዩም አልሄን ” (ጥቅስን በጥቅስ ውሰጥ እና ቀጥታና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)

ከዚያም ለባሪያዎችህ አልህ

ይሁዳ ራሱንና ወንድሞቹን እንደ “እርሱ ባሪያዎች” ያመለክታል፡፡ ይህ ትልቅ ባለሥልጣን ለሆነ ለአንድ ሰው የሚነገርለት መደበኛ መንገድ ነው፡፡ (አንደኛ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ወገን አገላለጽ ይመልከቱ)

ይዞ መውረድ …ወደ ታች መውረድ

ከከነዓን ወደ ግብጽ መጓዝ ሲነገር መውረድ የሚለው ቃል የተለመደ ነው::

ዳግመኛ ፊቴን አታዩም

እዚህ “ፊት” ሙሉ ሰውን ይወክላል:: አት እንደገና አታዩኝም (ምትክ ቃላት አጠቃቀም ይመልከቱ)

ከዚያም እንዲህ ሆነ

ይህ ሀረግ የተጠቀመው የታሪኩ አድስ ክፍል መጀመሩን ለማመለከት ነው:: በቋንቋዎ ይህን የሚገልጹበት መንገድ ካለ ይጠቀሙ:: (አድስ ክስተት ስለማስታወቅ ይመልከቱ)

ወደ ባሪያህ ወደ አባታችን በወጣን ጊዜ

ከግብጽ ወደ ከነዓን መጓዝ ሲነገር “ወደ ላይ መውጣት” የሚለውን ሀረግ መጠቀም የተለመደ ነው

የጌታዬን ቃል ነገርነው

ይሁዳ ዮሴፍን እንደ “ጌታዬ” ያመለክታል:: አት ጌታዬ የነገርከውን ቃል ነገርነው”(አንደኛ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ወገን አገላለጽ ይመልከቱ)

አባታችን ‘ተመልሳችሁ ጥቂት እህል ሸምቱልን አለ’

ይህ በጥቅስ ውስጥ ጥቅስ የያዘ ነው እንደ ተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊገለጽ ይችላል:: አት “አባታችን አንደገና ወደ ግብጽ በመሄድ ለእኛና ለቤተሰቦቻችን እህል እንድንሸምት ተናገረን ” (ጥቅስን በጥቅስ ውሰጥ እና ቀጥታና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)

እኛም አልነው ‘መሄድ አንችልም ታናሽ ወንድማችን ከእኛ ጋር…’

ይህ በጥቅስ ውስጥ ጥቅስ የያዘ ነው እንደ ተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊገለጽ ይችላል:: አት “ከዚያም ለእርሱ ወደ ግብጽ መውረድ አንችልም አልን ታናሽ ወንድማችን ከእኛ ጋር … ከእኛ ጋር ” (ጥቅስን በጥቅስ ውሰጥ እና ቀጥታና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)

የሰውየውን ፊት ማየት

እዚህ ፊት ሙሉ ሰውን ይወክላል:: አት “ሰውየውን ለማየት” (ምትክ ቃላት አጠቃቀም ይመልከቱ)

Genesis 44:27

ይሁዳ ታሪኩን ለዮሴፍ መናገርን ቀጠለ

እንዲህ አለን ሚስቴ ሁለት ወንዶች ልጆችን እንደወለደችልን እናንተ ታውቃላችሁ አንዱ ከእኔ ወጣ አውሬ በላው አላችሁኝ እስከ ዛሬም አላየሁትም ይህንም ከእኔ ለይታችሁ ደግሞ ብትወስዱ ክፉም ቢያገኘው ሽበቴን በሐዘን ወደ መቃበር ታወርዱታላችሁ ይህ ሁለት ደረጃና ሶስት ደረጃ ጥቅሶችን ይዞአል እነዚህም እንደተዘዋዋሪ ጥቅሶች ሊገለጹ ይችላሉ አት እንዲህ አለን ሚስቱ ራሔል ሁለት ወንዶች ልጆችን ብቻ እንደወለደችለት እናውቃለን ከእነርሱ አንዱ ወጣና አውሬ በላው እናም እስከ ዛሬ አላየሁትም ሌላውን ልጅ ብንወስደውና ክፉ ቢያገኘው በሐዘን እንዲሞት እናደርጋለን (ጥቅስን በጥቅስ ውሰጥ እና ቀጥታና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)ከዚይ አለ

እኛን እንዲህ አለን

እዚህ “እኛ” ዮሴፍን አያካትትም (ነጠላና ብዙ ወይም አካታች “እኛ” ይመልከቱ)

እናንተ ታውቃላችሁ

እዚህ “እናንተ” ብዙና ወንድሞቹን ያመለክታል (“እናንተ” አጠቃቀም ዓይነት ይመልከቱ)

በእውሬ ተበላ

ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል አት አውሬ በላው ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ

ጉዳት ቢደርስበት

ለአንድ ሰው አንድ ክፉ ነገር የሚደርሰበት ጉዳት ወደዚያ ሰው እንደሚመጣ ተደርጐ ተቆጥሮአል (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)

ሽበተን በሐዘን ወደ መቃብር ታወርዱታላችሁ

“ወደ መቃብር ማውረድ” እንዲሞትና ወደ መቃብር እንዲወርድ ማድረግ ማለት ነው:: “ማውረድ” የሚለውን ቃል የተጠቀመው መቃብር በመሬት ውስጥ እንደሆነ በተለምዶ የታወቀ ስለሆነ ነው:: አት “ከዚያም እኔን ሽማግሌውን በሐዘን እንዲሞት ታደርጋላችሁ” (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)

ሽበቴን

ያዕቆብን የሚያመለክትና ሽምግልናውን አበክሮ የሚናገር ነው:: አት “እኔ ሽማግለው” (ምትክ ቃል አጠቃቀም ይመልከቱ)

Genesis 44:30

አሁን

ይህ በዚህን ጊዜ ማለት አይደለም ነገር ግን ለሚቀጥለው ጠቃሚ ነገር ትኩረት እንዲሰጥበት ተጠቅሞአል

እንግዲህ በምንመለስበት ጊዜ … በሐዘን ወደ መቃብር

ይሁዳ ያለ ብንያምን ወደ አባቱ በሚመለስበት ጊዜ ምን ሊፈጠር እንደሚችል የሚገምተውን ነገር ግን እውነት የሆነውን ለዮሴፍ ይገልጻል (ግምታዊ ሁኔታዎችን ይመልከቱ)

ወደ ባሪያህ በሚመጣበት ጊዜ

እዚህ “መምጣት” “መሄድ” ወይም “መመለስ” በሚለው መተርጐም ይችላል::

ብላቴናው ከእኛ ጋር አለመኖር

ልጁ ከእኛ ጋር አለመኖር

ሕይወቱ ከልጁ ሕይወት ጋር የተሣሠረ ስለሆነ

አባታቸው ልጁ ከሞቴ እሞታለሁ ያለው አባባል የሁለቱ ሕይወት በአካል በጥብቅ የተሣሠረ እንደሆነ ተደርጐ ተገልጾአል:: አት “እርሱም ልጁ ካልተመለሰ እሞታለሁ ስላለ” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)

እንዲህም ሆነ

ይሁዳ ወደፊት ይሆናል ብሎ ስለሚገምተው ነገር በእርግጥ እደሚደረግ አድርጐ ይናገራል (ግምታዊ ሁኔታዎች ይመልከቱ)

ባሪያዎችህ የባሪያህን የአባታችንን ሽበት በሐዘን ወደ መቃብር ያወርዳሉ

ወደ መቃብር ማውረድ እንዲሞትና ወደ መቃብር እንዲወርድ ማድረግ ማለት ነው:: “ማውረድ” የሚለውን ቃል የተጠቀመው መቃብር በመሬት ውስጥ እንደሆነ በተለምዶ የታወቀ ስለሆነ ነው:: አት “እናም ሽማግሌውን አባታችንን በሐዘን እንዲሞት እናደርጋለን” (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)

ባሪያዎችህ ወይም አገልጋዮችህ

ይሁዳ ራሱንና ወንድሞችን “ባሪያዎችህ” ብሎ ያመለክታል:: ይህ ለአንድ ትልቅ ባለሥልጣን መደበኛ መንገድ የሚነገርለት ነው:: አት “እኛ አገልጋዮችህ” ወይም “እናም እኛ” (አንደኛ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ወገንነ ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)

የባሪያህን የአባታችንን ሽበት

እዚህ “ሽበት” ያዕቆብን የሚወክልና ሽምግልናውን የሚናገር ነው:: አት “ሽማግሌው አባታችን” (ምትክ ቃላት አጠቃቀም ይመልከቱ) ስለ ልጁ ደኀንነት በአባቴ ፊት ራሴን ዋስ አድርጌአለሁ ረቂቅ ስም ዋስ ተስፋ በሚለው ግሥ ሊገለጽ ይችላል አት ልጁን በሚመለከት ለአባቴ ተስፋ ስጥቼዋለሁ ረቂቅ ስሞች ይመልከቱ

ባሪያህ

ይሁዳ ራሱን “ባሪያህ” ብሎ ያመለክታል፡፡ አት “ለእኔ ለባሪያህ” ወይም “ለእኔ” (አንደኛ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)

በአባቴ ፊት በደሌን እሸከማለሁ

እንደበደለኛ መቆጠር በደል እንድሰው የሚሸከመው ነገር ተደርጐ ተገልጾአል:: አት “አባቴ ይወቅሰኛል” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)

Genesis 44:33

አሁን

ይህ በአሁን ጊዜ ማለት አይደለም ነገር ግን ለሚቀጥለው ዋና ነጥብ ትኩረት እንዲሰጥበት ተጠቅሞአል::

ባሪያህ

ይሁዳ ራሱን “ባሪያህ” ብሎ ያመለክታል፡፡ አት “እኔ ለባሪያህ” ወይም “እኔ” (አንደኛ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)

ልጁ… ይውጣ

ከግብጽ ወደ ከነዓን መጓዝ በሚነገርበት ጊዜ መውጣት የሚለውን ሀረግ መጠቀም የተለመደ ነበር

ልጁን ሳልይዝ እንዴት ተመልሼ ወደ አባቴ እሄዳለሁ?

ብንያምን ወደ ቤት ካልተመለሰ አባቱ ሊኖረው የሚችለውን ሐዘን ለማተኮር ይሁዳ ጥያቄ ይጠቀማል:: አት “ልጁ ከእኔ ጋር ካልሆነ ወደ አባቴ መመለስ እልችልም“ (አግናኝ ወይም ሽንገላ አዘል ጥያቄዎች ይመልከቱ)

በአባቶ ላይ የሚደርሰውን መከራ እንዳላይ

ከባድ መከራ የደረሰበት ሰው በዚያው ሰው ክፉ ነገር እንደመጣበት ተደርጐ ተነግሮአል (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)