አሁንም የሚለው ቃል የታሪኩን አዲስ ክፍል ያመለክታል (አድስ ክስተት ስለማስታወቅ ይመልከቱ)
ስለ እህል ምንም ባለማድረጋቸው ልጆቹን ለመቆጣት ያዕቆብ ጥያቄ ይጠቀማል:: አት “እዚሁ ዝም ብላችሁ አትቀመጡ” (ምትክ ቃላት የመጠቀም ዘይቤ ይመልከቱ)
ከከነዓን ወደ ግብጽ መሄድ ወደ ታች እንደመውረድ መናገር የተለመደ ነበር
እዚህ “ግብጽ” ሰዎች እህልን የሚሸጡበት ያመለክታል:: አት “በግብጽ እህልን ከሚሸጡ” (ምትክ ቃላት የመጠቀም ዘይቤ ይመልከቱ)
ብንያምና ዮሴፍ አንድ አባትና እናት ነበራቸው የዕቆብ የራሔል መጨረሻ ልጅዋ እንዲጐዳ ወይም ክፉ ነገር እንዲደርስበት አልፈለገም ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይጠቀሙ
“መጡ” የሚለው ቃል “ሄዱ” በሚለው ሊተረጐም ይችላል:: እንዲሁም እህል እና ግብጽ የተባሉ ቃላት የታወቁ ናቸው:: አት “የእስራኤል ልጆች እህል ለመሸመት ከሌሎች ሰዎች ጋር ወደ ግብጽ ሄዱ” (ሄደ እና መጣ አጠቃቀምና ድብቅ ቃላት የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
“በዚህን ጊዜ” ታሪኩ ወደ ዮሴፍ ሕይወት መረጃ መቀየሩን ያመለክታል:: (የዳራ መረጃ ይመልከቱ)
ምድር ግብጽን ያመለክታል:: አት “በግብጽ ላይ” (ግምታዊ እውቀት ወይም ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)
እዚህ አገር ግብጽንና ዙሪያው ያሉ አገሮችን ያጠቃልላል አት እህል ለመሸመት ከተለያዩ አገሮች ለመጡ ሰዎች ሁሉ (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)
“መጡ” እንደ “ሄዱ” ሊተረጐም ይችላል:: (መጣ እና ሄደ አጠቃቀም ይመልከቱ)
ይህ አክብሮትን የመስጠት ምልክት ነው:: (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)
ዮሴፍም ወንድዋቹን ባያቸው ጊዜ አወቃቸው
“የእነርሱ ወንድም እንዳልሆነ ታየ” ወይም “ወንድማቸው እንደሆነ እንዲያውቁት አልፈለገም”
ዮሴፍ መልሱን ቢያውቅም ይህ አግናኝ ጥያቄ አልነበረም የራሱን ማንነት ለወንድሞቹ ላለመግለጽ የመረጠው መንገድ ነበር
ሰላዮች ሌላ አገርን ለመጥቅ በስውር ስለአንድ አገር መረጃ ለማግኘት የሚጥሩ ሰዎች ናቸው::
የዚህ ሙሉ ትርጉም ግልጽ ሊደረግ ይችላል አት አገራችን በየትኛው በኩል እንደተጋለጠች ለማየትና ከዚያም ሊታጠቁን ለማየት መጥታችኋል (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)
አንድን ሰው ለማክበር የሚጠቀሙበት አባባል ነው
ወንድሞቹ ራሳቸውን እንደ ባሪያዎች አድርገው ያቀርባሉ፡፡ ይህም ከፍተኛ ሥልጣን ላለው ሰው የሚነገርለት መደበኛ መንገድ ነው፡፡አት “እኛ ባሪያዎችህ” ወይም “እኛ” (አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)
ዮሴፍ ለወንድሞቹ አላቸው
የዚህ ሙሉ ትርጉም ግልጽ ሊደረግ ይችላል:: አት “አይደለም በየት በኩል ምድራችን ለጥቃት የተጋለጠች መሆንዋን ለመሰለልና ከዚያም ሊታጠቁን ነው” (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)
12ቱ ወንድሞች (ቁጥሮችን ይመልከቱ)
“ስማን ትንሹ ወንድማችን” “እየው” የሚለው ቃል ቀጥለው ለምነግሩት ነገር ትኩረት እንዲሰጥ ተጠቅሞአል::
“በዚህን ጊዜ ትንሹ ወንድማችን ከአባታችን ጋር ነው”
“እንደነገርኋችሁ ሰላዮች ናችሁ” (በዘፍጥረት 42;9 “ሰላዮች” እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ)
ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “የሚፈትናችሁ በዚህ ነው” (ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)
ይህ ጠንከር ወይም ኮስተር ያለ መሃላ ነው አት በፈርዖን ሕይወት እምላለሁ
“ከእናንተ አንዱን ምረጡና ሂዶ ወንድማችሁን ይዞ ይመለስ”
የቀራችሁ በእሥር ቤት ትቆያላችሁ
ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል አት እውነት መናገራችሁን እንዳውቅ (ተሻጋሪ ግሥና የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልክቱ)
በእስር ቤት
“ሶስት” የሚለው ተራ ቁጥር ነው:: አት “ከሁለተኛው ቀን በኋላ” (መቁጠሪያ ተራ ቁጥሮችን ይመልከቱ)
የተቀመጠው መረጃ ግልጽ ሊደረግ ይችላል:: አት “የሚለውን ካደረጋችሁ በሕይወት ትተርፉ አደርጋችኋለሁ” (የተደበቁ ቃላትን ስለመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
ይህ ከልብ እግዚአብሔርን ማክበርንና ያንን ለእርሱ በመታዘዝ መግለጽን ያመለክታል
ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ልገለጽ ይችላል:: አት “እንዱን ወንድማችሁን እዚሁ እሥር ቤት ተውት” (ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)
እዚህ ሂዱ ብዙ አመላካችና በእሥር ቤት የማይቆዩ ወንድሞች ሁሉን ያመለክታል (ብዙ አመላካች እናንተ ይመልከቱ)
እዚህ ቤቶች ቤተሰቦችን ይወክላል:: አት “በዚህ ራብ ወቅት ቤተሰቦቻችሁን ለመርዳት እህል ትወስዱላቸዋላችሁ” (ምትክ ቃላት የመጠቀም ዘይቤ ይመልከቱ)
ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል አት የሚትነግሩ እውነት መሆኑን አውቃለሁ (ተሻጋሪ ግሥና የማይሻገር ግሥ ይመልከቱ)
ወንድሞቹ ሰላይ መሆናቸውን ካረጋገጠ ዮሴፍ በወታደሮቹ እንደሚያስገድላቸው የሚል ትርጉም ይኖረዋል:: (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)
ነፍሱ ዮሴፍን ይወክላል አት ዮሴፍ እንደዚያ ሲጨነቅ አይተን ወይም ዮሴፍ እንደዚያ ሲሰቃይ አይተን (ክፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን እንደ ክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
“ጭንቀት” የሚለው ረቂቅ ስም “መከራ” በሚለው ግሥ ሊተረጐም ይችላል:: አት “ይህ መከራ የደረሰብን በዚሁ ምክንያት ነው” (ረቂቅ ስሞች ይመልከቱ)
ይህ በጥቅስ ውስጥ ጥቅስ ይዞአል እንደ ተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊገልጽ ይችላል:: አት “በዚህ ልጅ ላይ ኃጢአት እንዳታደርጉ አልነገርኋችሁምን፤ነገር ግን” ወይም “ልጁ ላይ ክፉ እንዳታደርጉ ነግሬአችኋለሁ፤ ነገር ግን” (በጥቅሶች ውስጥ ጥቅሶችንና ቀጥተኛና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)
እዚህ አሁን በዚህን ጊዜ ማለት አይደለም አሁን እና እዩ ሁለቱ የተጠቀሙት ለሚቀጥለው በጣም ጠቃሚ ነጥብ ትኩረት እንዲሰጥበት ነው
እዚህ ደም የዮሴፍን ሞት ይወክላል ወንድምቹ ዮሴፍ እንደሞተ አስበዋል:: “ከእጃችን ይፈለጋል” የሚለው ሀረግ ስላደረጉት ነገር ይቀጣሉ ማለት ነው:: አት “ለሞቱ የሚገባውን ቅጣት እየተቀበልን ነን” ወይም “በመግደላችን መከራ እየተቀበልን ነን” (ምትክ ቃላት የመጠቀም ዘይቤ ወይም ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)
አስተርጓሚ አንድ ሰው የሚናገረውን ወደ ሌላ ቋንቋ የሚተረጉም ሰው ማለት ነው ዮሴፍ የእነርሱን ቋንቋ እንደማይናገር ለማስመሰል በራሱና በእነርሱ መካከል አስተርጓሚ አድርጐ ነበር
ዮሴፈ ወንድሞቹ የተናገሩትን በመስማቱ ስሜቱ ስለተነካ አለቀሰ (ግምታዊ እውቀት ወይም ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)
እስከዚህ ዮሴፍ ወንድሞቹን የሚያናግረው በተለየ ቋንቋ ስለሆነ አስተርጓሚ ይጠቀም ነበር (ግምታዊ እውቀት ወይም ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)
እዚህ ለሚያዩት ነገር ትኩረት ለመስጠት ሰዎች በዐይኖች ተመስለዋል:: አት “በፊታቸው አሰረው” (ክፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን እንደ ክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
ለጉዞአቸው ስንቅ እንዲሰጡአቸው
ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል አት ዮሴፍ ያዘዘውን ሁሉ አገልጋዮቹ አደረጉላቸው (ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)
በመንገድም አዳር ሰፍረው ሳሉ ከእነርሱ አንዱ ከያዘው እህል ላይ ለአህያው ለመስጠት ስልቻውን ሲፈታ በስልቻው አፍ ላይ ብሩን አየ
እዚህ እነሆ የሚለው ቃል ለሚቀጥለው አስገራሚ ሃሳብ ትኩረት እንድንሰጥ ለማድረግ ነው
ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልከ ሊገለጽ ይችላል አት አንድ ሰው ብሬን መልሳ አስቀመጠልኝ (ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልክቱ)
ይሄው በስልቻዬ እዩ
መፍራቻው ልባቸው በድንጋጤ እንደተዋጠ እንደተሞላ ተገልጾአል እዚህ ልብ በድፍረት ተመስሎአል አት እጅግ በጣም ፈሩ
የግብጽ ጌታ
በክፉ ንግግር ተናገረን
ሰላዮች ሌላን አገር ለመጥቀም ሰለአንድ አገር በሚስጢር መረጃ የሚሰበስቡ ሰዎች ናቸው:: በዘፍጥረት 42 9 ሰላዮች የሚለውን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱእኛም እንዲህ አልነው እኛ የታመንን ሰዎች ነን፡፡ ሰላዮች አይደለንም፡፡ እኛ የአንድ አባት ልጆች የሆንን አሥራ ሁለት ወንድማማቾች ነን፡፡ እንዱ በሕይወት የለም …..በከነዓን ይገኛል ይህ በጥቅስ ውስጥ የሚገኝ ጥቅስ ይዞአል ይህም እንደተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊጠቀስ ይችላል:: አት እኛ የታመንን ሰዎች እንጂ ሰላዮች አይደለንም:: እኛ የአንድ አባት ልጆች የሆንን አሥራ ሁለት ወንድማማቾች ነን:: አንዱ በሕይወት የለም … በከነዓን ይገኛል (በጥቅስ ውስጥ ያሉ ጥቅሶች ቀጥተኛና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)
“ወንድም” የሚለው ቃል የታወቀ ነው አት “አንዱ ወንድማችን በሕይወት የለም” (የተደበቁ ቃላትን የመግለጽ ዘይቤ ይጠቀሙ)
“ወንድም” የሚለው ቃል የታወቀ ነው:: አት “ታናሽ ወንድማችን…. ዛሬ ከአባታችን ጋር አለ” (የተደበቁ ቃላትን የመግለጽ ዘይቤ ይጠቀሙ)
የግብጽ ጌታ
ቤቶች ቤተሰብን ይወክላሉ አት በራብ ወቅት ቤተሰባችሁን ለመርዳት እህል ይዛችሁላችሁ ሂዱ (ምትክ ቃላት ስለመጠቀም ይመልከቱ)
ወደ ቤታችሁ ሂዱ ወይም ሂዱ
በምድሪቱ እንዲትሸጡና እንዲትገዙ እፈቅድላችኋለሁ
ይህ ሀረግ እዚህ የተጠቀመው በታሪኩ ጠቃሚ ክሰተት ለማመልከት ነው በቋንቋዎ ይህን መግለጽ የማችሉበት መንገድ ካለ በዚህ ቦታ ሊጠቀሙ ይችላሉ
ተገረሙ ምክንያቱም እያንዳንዳቸው
ያለ ልጅ እኮ አስቀራችሁኝ ወይም ሁለቱን ልጆች እንዳጣ አደረጋችሁኝ
እነዚህ ሁሉ ጐዱኝ
ይህ አብሮ እንዲሄድ ብንያምን እንዲሰጠውና በጉዞው እንደሚጠነቀቅለት ሮቤል የጠየቀው ጥያቄ ነው አት ለእርሱ ኃላፊነት ስጠኝ ወይም ለእርሱ እኔ ሊጠነቀቅለት ዘይቤያዊ አነጋገር ይጠቀሙ
ከከነዓን ወደ ግብጽ ጉዞ ስታሰብ እዚህ የተጠቀመው ወደታች መውረድ የሚለው አባባል የተለመደ ነው አት ልጄ ብንያምን አብሮአችሁ ወደ ግብጽ አይሄድም
እዚህ እናንተ ብዙን የሚያመለክትና የያዕቆብን ልጆች የሚገልጽ ነው( “እናንተ” አጠቃቀም ይመልከቱ)
የዚህ ሙሉ ትርጉም ግልጽ ሊደረግ ይችላል:: አት “ባለቤቴ ራሔል ሁለትልጆች ነበራት ዮሴፍ ሞቶአልና ብንያም ብቻውን ቀርቶአል” (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)
“ወደ ግብጽ ስትሄዱና ስትመለሱ” ወይም “ርቃችሁ ስትሄዱ” እዚህ “መንገድ” “ጉዞን” ያመለክታል
ወደ መቃብር ታወርዱታለችሁ እንዲሞትና ወደ መቃብር እንዲወርድ ታደርጉታላችሁ የሚል አባባል ነው:: መቃብር በተለምዶ እንደሚታመነው ከምድር በታች ስለሆነ ታወርዱታላችሁ የሚለውን ቃል ይጠቀማል:: አት “እኔን ሽማግሌውን በሐዘን እንድሞት ታደርጉታላችሁ” (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ይህ ያዕቆብን የሚያመለክትና ሽምግልና ዕድሜውን የሚገልጽ ነው አት “እኔ ሽማግሌ ሰው” (ክፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን እንደ ክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)