Genesis 42

Genesis 42:1

አሁንም ያዕቆብ ….እንዲህ አላቸው

አሁንም የሚለው ቃል የታሪኩን አዲስ ክፍል ያመለክታል (አድስ ክስተት ስለማስታወቅ ይመልከቱ)

ለምን እርስበርስ ትተያያላችሁ?

ስለ እህል ምንም ባለማድረጋቸው ልጆቹን ለመቆጣት ያዕቆብ ጥያቄ ይጠቀማል:: አት “እዚሁ ዝም ብላችሁ አትቀመጡ” (ምትክ ቃላት የመጠቀም ዘይቤ ይመልከቱ)

ወደዚያ ይውረዱ …. ወረዱ

ከከነዓን ወደ ግብጽ መሄድ ወደ ታች እንደመውረድ መናገር የተለመደ ነበር

ከግብጽ

እዚህ “ግብጽ” ሰዎች እህልን የሚሸጡበት ያመለክታል:: አት “በግብጽ እህልን ከሚሸጡ” (ምትክ ቃላት የመጠቀም ዘይቤ ይመልከቱ)

ያዕቆብ የዮሴፍን ወንድም ብንያምን … አልላከውም

ብንያምና ዮሴፍ አንድ አባትና እናት ነበራቸው የዕቆብ የራሔል መጨረሻ ልጅዋ እንዲጐዳ ወይም ክፉ ነገር እንዲደርስበት አልፈለገም ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይጠቀሙ

Genesis 42:5

የእስራኤል ልጆች ለእህል ሸመታ ከመጡበት ጋር

“መጡ” የሚለው ቃል “ሄዱ” በሚለው ሊተረጐም ይችላል:: እንዲሁም እህል እና ግብጽ የተባሉ ቃላት የታወቁ ናቸው:: አት “የእስራኤል ልጆች እህል ለመሸመት ከሌሎች ሰዎች ጋር ወደ ግብጽ ሄዱ” (ሄደ እና መጣ አጠቃቀምና ድብቅ ቃላት የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)

በዚህን ጊዜ ዮሴፍ

“በዚህን ጊዜ” ታሪኩ ወደ ዮሴፍ ሕይወት መረጃ መቀየሩን ያመለክታል:: (የዳራ መረጃ ይመልከቱ)

በምድሪቱ ላይ

ምድር ግብጽን ያመለክታል:: አት “በግብጽ ላይ” (ግምታዊ እውቀት ወይም ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)

ለአገሩ ሰዎች ሁሉ

እዚህ አገር ግብጽንና ዙሪያው ያሉ አገሮችን ያጠቃልላል አት እህል ለመሸመት ከተለያዩ አገሮች ለመጡ ሰዎች ሁሉ (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)

የዮሴፍም ወንድሞች መጡ

“መጡ” እንደ “ሄዱ” ሊተረጐም ይችላል:: (መጣ እና ሄደ አጠቃቀም ይመልከቱ)

በግምባራቸው ወደ ምድር ጐንበስ ብለው ሰገዱለት

ይህ አክብሮትን የመስጠት ምልክት ነው:: (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)

Genesis 42:7

ዮሴፍም ወንድሞቹን አይቶ አወቃቸው

ዮሴፍም ወንድዋቹን ባያቸው ጊዜ አወቃቸው

እንደማያውቃቸው ሆነ

“የእነርሱ ወንድም እንዳልሆነ ታየ” ወይም “ወንድማቸው እንደሆነ እንዲያውቁት አልፈለገም”

ከየት የመጣችሁ ናችሁ?

ዮሴፍ መልሱን ቢያውቅም ይህ አግናኝ ጥያቄ አልነበረም የራሱን ማንነት ለወንድሞቹ ላለመግለጽ የመረጠው መንገድ ነበር

Genesis 42:9

ሰላዮች ናችሁ

ሰላዮች ሌላ አገርን ለመጥቅ በስውር ስለአንድ አገር መረጃ ለማግኘት የሚጥሩ ሰዎች ናቸው::

ምድሪቱ በየትኛ በኩል የተጋለጠች እንደሆነች ሊታዩ መጥታችኋል

የዚህ ሙሉ ትርጉም ግልጽ ሊደረግ ይችላል አት አገራችን በየትኛው በኩል እንደተጋለጠች ለማየትና ከዚያም ሊታጠቁን ለማየት መጥታችኋል (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)

ጌታችን ሆይ

አንድን ሰው ለማክበር የሚጠቀሙበት አባባል ነው

ባሪያዎችህ

ወንድሞቹ ራሳቸውን እንደ ባሪያዎች አድርገው ያቀርባሉ፡፡ ይህም ከፍተኛ ሥልጣን ላለው ሰው የሚነገርለት መደበኛ መንገድ ነው፡፡አት “እኛ ባሪያዎችህ” ወይም “እኛ” (አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)

Genesis 42:12

እርሱ ለእነርሱ አላቸው

ዮሴፍ ለወንድሞቹ አላቸው

አይደለም በየት በኩል ምድራችን ጥቃት የተጋለጠች መሆንዋን ለማየት ነው

የዚህ ሙሉ ትርጉም ግልጽ ሊደረግ ይችላል:: አት “አይደለም በየት በኩል ምድራችን ለጥቃት የተጋለጠች መሆንዋን ለመሰለልና ከዚያም ሊታጠቁን ነው” (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)

አሥራ ሁለቱ ወንድሞች

12ቱ ወንድሞች (ቁጥሮችን ይመልከቱ)

እየው ትንሹ ወንድማችን

“ስማን ትንሹ ወንድማችን” “እየው” የሚለው ቃል ቀጥለው ለምነግሩት ነገር ትኩረት እንዲሰጥ ተጠቅሞአል::

ትንሹ ወንድማችን አባታችን ዘንድ ነው

“በዚህን ጊዜ ትንሹ ወንድማችን ከአባታችን ጋር ነው”

Genesis 42:14

ነገርኋች እኮ ሰላዮች ናችሁ

“እንደነገርኋችሁ ሰላዮች ናችሁ” (በዘፍጥረት 42;9 “ሰላዮች” እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ)

በዚህ ትፈተናላችሁ

ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “የሚፈትናችሁ በዚህ ነው” (ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)

በፈርዖን ሕይወት

ይህ ጠንከር ወይም ኮስተር ያለ መሃላ ነው አት በፈርዖን ሕይወት እምላለሁ

ከእናንተ አንዱን ላኩና ወንድማችሁን ይዞ ይመለስ

“ከእናንተ አንዱን ምረጡና ሂዶ ወንድማችሁን ይዞ ይመለስ”

እስር ቤት ትቆያላችሁ

የቀራችሁ በእሥር ቤት ትቆያላችሁ

የተናገራችሁት ቃል እውነት መሆኑ እስኪረጋገጥ

ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል አት እውነት መናገራችሁን እንዳውቅ (ተሻጋሪ ግሥና የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልክቱ)

በግዞት ቤት

በእስር ቤት

Genesis 42:18

በሶስተኛውም ቀን

“ሶስት” የሚለው ተራ ቁጥር ነው:: አት “ከሁለተኛው ቀን በኋላ” (መቁጠሪያ ተራ ቁጥሮችን ይመልከቱ)

እንዲህ በማድረግ ሕይወታችሁን አትርፉ

የተቀመጠው መረጃ ግልጽ ሊደረግ ይችላል:: አት “የሚለውን ካደረጋችሁ በሕይወት ትተርፉ አደርጋችኋለሁ” (የተደበቁ ቃላትን ስለመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)

እግዚአብሔርን እፈራለሁና

ይህ ከልብ እግዚአብሔርን ማክበርንና ያንን ለእርሱ በመታዘዝ መግለጽን ያመለክታል

አንዱ ወንድማችሁ በእሥር ቤት ይቆይ

ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ልገለጽ ይችላል:: አት “እንዱን ወንድማችሁን እዚሁ እሥር ቤት ተውት” (ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)

እናንተ ግን ሂዱ

እዚህ ሂዱ ብዙ አመላካችና በእሥር ቤት የማይቆዩ ወንድሞች ሁሉን ያመለክታል (ብዙ አመላካች እናንተ ይመልከቱ)

ለተራቡት ቤተሰቦቻችሁ እህል ትወስዱላቸዋላችሁ

እዚህ ቤቶች ቤተሰቦችን ይወክላል:: አት “በዚህ ራብ ወቅት ቤተሰቦቻችሁን ለመርዳት እህል ትወስዱላቸዋላችሁ” (ምትክ ቃላት የመጠቀም ዘይቤ ይመልከቱ)

የተናገራችሁት ቃል እውነተኛነት ይረጋገጣል

ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል አት የሚትነግሩ እውነት መሆኑን አውቃለሁ (ተሻጋሪ ግሥና የማይሻገር ግሥ ይመልከቱ)

ከሞት ትተርፋላችሁ

ወንድሞቹ ሰላይ መሆናቸውን ካረጋገጠ ዮሴፍ በወታደሮቹ እንደሚያስገድላቸው የሚል ትርጉም ይኖረዋል:: (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)

Genesis 42:21

ነፍሱ ስትጨነቅ አይተን

ነፍሱ ዮሴፍን ይወክላል አት ዮሴፍ እንደዚያ ሲጨነቅ አይተን ወይም ዮሴፍ እንደዚያ ሲሰቃይ አይተን (ክፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን እንደ ክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)

ይህ ጭንቀት የደረሰብን በዚህ ምክንያት ነው

“ጭንቀት” የሚለው ረቂቅ ስም “መከራ” በሚለው ግሥ ሊተረጐም ይችላል:: አት “ይህ መከራ የደረሰብን በዚሁ ምክንያት ነው” (ረቂቅ ስሞች ይመልከቱ)

በዚህ ልጅ ላይ ክፉ አታድርጉ ብዬ አልነበረምን? እናንተ ግን አልሰማችሁኝም

ይህ በጥቅስ ውስጥ ጥቅስ ይዞአል እንደ ተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊገልጽ ይችላል:: አት “በዚህ ልጅ ላይ ኃጢአት እንዳታደርጉ አልነገርኋችሁምን፤ነገር ግን” ወይም “ልጁ ላይ ክፉ እንዳታደርጉ ነግሬአችኋለሁ፤ ነገር ግን” (በጥቅሶች ውስጥ ጥቅሶችንና ቀጥተኛና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)

አሁንም እዩ

እዚህ አሁን በዚህን ጊዜ ማለት አይደለም አሁን እና እዩ ሁለቱ የተጠቀሙት ለሚቀጥለው በጣም ጠቃሚ ነጥብ ትኩረት እንዲሰጥበት ነው

ደሙ ከእጃችን ይፈለጋል

እዚህ ደም የዮሴፍን ሞት ይወክላል ወንድምቹ ዮሴፍ እንደሞተ አስበዋል:: “ከእጃችን ይፈለጋል” የሚለው ሀረግ ስላደረጉት ነገር ይቀጣሉ ማለት ነው:: አት “ለሞቱ የሚገባውን ቅጣት እየተቀበልን ነን” ወይም “በመግደላችን መከራ እየተቀበልን ነን” (ምትክ ቃላት የመጠቀም ዘይቤ ወይም ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)

Genesis 42:23

በመካከላቸው አስተርጓሚ ነበረና …. አላወቁም

አስተርጓሚ አንድ ሰው የሚናገረውን ወደ ሌላ ቋንቋ የሚተረጉም ሰው ማለት ነው ዮሴፍ የእነርሱን ቋንቋ እንደማይናገር ለማስመሰል በራሱና በእነርሱ መካከል አስተርጓሚ አድርጐ ነበር

ከእነርሱ ዘወር ብሎ አለቀሰ

ዮሴፈ ወንድሞቹ የተናገሩትን በመስማቱ ስሜቱ ስለተነካ አለቀሰ (ግምታዊ እውቀት ወይም ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)

ተናገራቸው

እስከዚህ ዮሴፍ ወንድሞቹን የሚያናግረው በተለየ ቋንቋ ስለሆነ አስተርጓሚ ይጠቀም ነበር (ግምታዊ እውቀት ወይም ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)

ዐይናቸው እያየ አሠረው

እዚህ ለሚያዩት ነገር ትኩረት ለመስጠት ሰዎች በዐይኖች ተመስለዋል:: አት “በፊታቸው አሰረው” (ክፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን እንደ ክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)

የመንገድ ስንቅ ይሰጡአቸው ዘንድ

ለጉዞአቸው ስንቅ እንዲሰጡአቸው

ይህም ተደረገላቸው

ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል አት ዮሴፍ ያዘዘውን ሁሉ አገልጋዮቹ አደረጉላቸው (ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)

Genesis 42:26

ከእነርሱም አንዱ በአደረበት ሥፍራ ለአህያው ገፈራን ሊሰጥ ዘንድ ዓይበቱን ሲፈታ ብሩን አየ እነሆም በዓይበቱ አፍ ላይ ነበረች

በመንገድም አዳር ሰፍረው ሳሉ ከእነርሱ አንዱ ከያዘው እህል ላይ ለአህያው ለመስጠት ስልቻውን ሲፈታ በስልቻው አፍ ላይ ብሩን አየ

እነሆ

እዚህ እነሆ የሚለው ቃል ለሚቀጥለው አስገራሚ ሃሳብ ትኩረት እንድንሰጥ ለማድረግ ነው

ብሬ ተመልሶልኛል

ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልከ ሊገለጽ ይችላል አት አንድ ሰው ብሬን መልሳ አስቀመጠልኝ (ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልክቱ)

ይሄው ወደዚህ እዩ

ይሄው በስልቻዬ እዩ

ልባቸው በድንጋጤ ተሞላ

መፍራቻው ልባቸው በድንጋጤ እንደተዋጠ እንደተሞላ ተገልጾአል እዚህ ልብ በድፍረት ተመስሎአል አት እጅግ በጣም ፈሩ

Genesis 42:29

የአገሩ ጌታ

የግብጽ ጌታ

በቁጣ ተናገረን

በክፉ ንግግር ተናገረን

ሰላዮች እንደሆንን

ሰላዮች ሌላን አገር ለመጥቀም ሰለአንድ አገር በሚስጢር መረጃ የሚሰበስቡ ሰዎች ናቸው:: በዘፍጥረት 42 9 ሰላዮች የሚለውን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱእኛም እንዲህ አልነው እኛ የታመንን ሰዎች ነን፡፡ ሰላዮች አይደለንም፡፡ እኛ የአንድ አባት ልጆች የሆንን አሥራ ሁለት ወንድማማቾች ነን፡፡ እንዱ በሕይወት የለም …..በከነዓን ይገኛል ይህ በጥቅስ ውስጥ የሚገኝ ጥቅስ ይዞአል ይህም እንደተዘዋዋሪ ጥቅስ ሊጠቀስ ይችላል:: አት እኛ የታመንን ሰዎች እንጂ ሰላዮች አይደለንም:: እኛ የአንድ አባት ልጆች የሆንን አሥራ ሁለት ወንድማማቾች ነን:: አንዱ በሕይወት የለም … በከነዓን ይገኛል (በጥቅስ ውስጥ ያሉ ጥቅሶች ቀጥተኛና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)

አንዱ በሕይወት የለም

“ወንድም” የሚለው ቃል የታወቀ ነው አት “አንዱ ወንድማችን በሕይወት የለም” (የተደበቁ ቃላትን የመግለጽ ዘይቤ ይጠቀሙ)

ታናሹም ….ዛሬ ከአባታችን ጋር አለ

“ወንድም” የሚለው ቃል የታወቀ ነው:: አት “ታናሽ ወንድማችን…. ዛሬ ከአባታችን ጋር አለ” (የተደበቁ ቃላትን የመግለጽ ዘይቤ ይጠቀሙ)

Genesis 42:33

የአገሩ ጌታ

የግብጽ ጌታ

ለተራቡት ቤተሰቦቻችሁ እህል ይዛችሁላችሁ ሂዱ

ቤቶች ቤተሰብን ይወክላሉ አት በራብ ወቅት ቤተሰባችሁን ለመርዳት እህል ይዛችሁላችሁ ሂዱ (ምትክ ቃላት ስለመጠቀም ይመልከቱ)

መንገዳችሁን ሂዱ

ወደ ቤታችሁ ሂዱ ወይም ሂዱ

እናንተም በምድሪቱ ትነግዳላችሁ

በምድሪቱ እንዲትሸጡና እንዲትገዙ እፈቅድላችኋለሁ

Genesis 42:35

እንዲህም ሆነ

ይህ ሀረግ እዚህ የተጠቀመው በታሪኩ ጠቃሚ ክሰተት ለማመልከት ነው በቋንቋዎ ይህን መግለጽ የማችሉበት መንገድ ካለ በዚህ ቦታ ሊጠቀሙ ይችላሉ

እነሆ እያንዳንዳቸው

ተገረሙ ምክንያቱም እያንዳንዳቸው

ልጅ አልባ አስቀራችሁኝ

ያለ ልጅ እኮ አስቀራችሁኝ ወይም ሁለቱን ልጆች እንዳጣ አደረጋችሁኝ

ይህ ሁሉ በእኔ ላይ ደረሰ

እነዚህ ሁሉ ጐዱኝ

Genesis 42:37

እርሱን በእጄ ስጠኝ

ይህ አብሮ እንዲሄድ ብንያምን እንዲሰጠውና በጉዞው እንደሚጠነቀቅለት ሮቤል የጠየቀው ጥያቄ ነው አት ለእርሱ ኃላፊነት ስጠኝ ወይም ለእርሱ እኔ ሊጠነቀቅለት ዘይቤያዊ አነጋገር ይጠቀሙ

ልጄ ወደዚያው አብሮአችሁ አይወርድም

ከከነዓን ወደ ግብጽ ጉዞ ስታሰብ እዚህ የተጠቀመው ወደታች መውረድ የሚለው አባባል የተለመደ ነው አት ልጄ ብንያምን አብሮአችሁ ወደ ግብጽ አይሄድም

ከእናንተ ጋር

እዚህ እናንተ ብዙን የሚያመለክትና የያዕቆብን ልጆች የሚገልጽ ነው( “እናንተ” አጠቃቀም ይመልከቱ)

ወንድሙ እንደሆነ ሞቶአል የቀረው እርሱ ብቻ ነው

የዚህ ሙሉ ትርጉም ግልጽ ሊደረግ ይችላል:: አት “ባለቤቴ ራሔል ሁለትልጆች ነበራት ዮሴፍ ሞቶአልና ብንያም ብቻውን ቀርቶአል” (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)

ስትሄዱ በመንገድ ላይ

“ወደ ግብጽ ስትሄዱና ስትመለሱ” ወይም “ርቃችሁ ስትሄዱ” እዚህ “መንገድ” “ጉዞን” ያመለክታል

ሽበቴን በመሪር ሐዘን ወደ መቃብር ታወርዱታላችሁ

ወደ መቃብር ታወርዱታለችሁ እንዲሞትና ወደ መቃብር እንዲወርድ ታደርጉታላችሁ የሚል አባባል ነው:: መቃብር በተለምዶ እንደሚታመነው ከምድር በታች ስለሆነ ታወርዱታላችሁ የሚለውን ቃል ይጠቀማል:: አት “እኔን ሽማግሌውን በሐዘን እንድሞት ታደርጉታላችሁ” (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)

ሽበቴን

ይህ ያዕቆብን የሚያመለክትና ሽምግልና ዕድሜውን የሚገልጽ ነው አት “እኔ ሽማግሌ ሰው” (ክፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን እንደ ክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)