Genesis 41

Genesis 41:1

እንዲህም ሆነ

ይህ ሀረግ የታሪኩ አድስ ክፍል መጀመሩን ያመለክታል በቋንቋዎ ይህን የሚገልጹበት መንገድ ካለ ያን ሊጠቀሙ ይችላሉ (አዲስ ክስተትን ማስታወቅ ይመልከቱ)

ድፍን ሁለት ዓመታት ካለፈ በኋላ

በእስር ቤት ከዮሴፍ አብረውት ስለነበሩት የፈርዖን መጠጥ አሳላፊዎች አለቃና እንጀራ ቤት አዛዥ ሕልሞችን ዮሴፍ ከተረጐመላቸው ሁለት ዓመታት ካለፊ በኋላ

እነሆም ቆሞ ነበር

እዚህ እነሆ የሚለው ቃል በሰፊው ታሪክ ሌላ ክስተት መጀመሩን ያመለክታል በቋንቋዎ ይህን የሚገልጹበት መንገድ ሊኖር ይችላል፡፡ አት “ቆሞ በመገኘቱ ገርሞት ነበር”

ቆሞ ነበር

ፈርዖ ቆሞ ነበር

መልካምና የወፈሩ

ጤናማና የወፈሩ

በውሃውም ዳር ባለው ቀጠማ ተሰማርተው ነበር

በወንዙ ዳር የበቀለውን ሣር ይበሉ ነበር

ቀጤማ

በረግረጋማ ቦታ የሚበቅል ቀጭንና ረጅም ሣር ነው

እነሆ ሌሎች ሰባት ላሞች

እዚህ እነሆ የሚለው ቃል ፈረዖን እንደገና ባየው ነገር እንደተገረመ ያሳያል

የከፉና የከሱ

ታማሚና የከሱ

ወንዝ ዳር

“በወንዝ ዳር” ወይም “ወንዝ ዳረቻ ላይ” ይህ በአንድ ወንዝ ዳር ጠርዝ የሚገኝ ከፍታ ያለው መሬት ማለት ነው::

Genesis 41:4

የከፉና የከሱ

“ደካማና የከሱ” በዘፍጥረት 41:3 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ::

መልካምና የወፈሩ

“ጤናማና የደለቡ ወይም በደንብ የበሉ” በዘፍጥረት 41:2 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ::

ነቃ

ከእንቅልፉ ነቃ

ሁለተኛ ጊዜ

“ሁለት” የሚለው ቃል ተራ ቁጥር ሁለት ነው:: አት “እንደገና” (ተራ ቁጥሮችን ይመልከቱ)

እነሆ ዛላዎች

እዚህ እነሆ የሚለው ቃል ፈርዖን ባየው ነገር እንደተገረመ የሚያሳይ ነው

የእሸት ዛላዎች

ዛላዎች ፍሬዎች የሚንዠረግጉበት የበቆሎ ተክል አካል ነው

በአንድ የእህል አገዳ ላይ

“በአንድ አገዳ ላይ ያፌራውን ወይም የተንዠረገገውን” አገዳ ወፍራምና ረጅም የተክል ክፍል ነው::

በአንዱ አገዳ ላይ የተንዠረገገና ያማረ

በአንድ አገዳ ጤናማና ያማረ

የቀጨጩና በምሥራቅ ንፋስ የተመቱ

ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊተረጐም ይችላል:: አት: “ያም ከምሥራቅ ደረቅ አየር የትነሳ የቀጨጩና በዋግ የተመቱ” (ተሻጋሪ ግሥና የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)

የምሥራቅ ንፋስ

የምሥራቅ ንፋስ ከረሃማ ተነሥቶ የሚነፍስ ነው፡፡ የምስራቅ ንፋስ ሙቀት እጅግ ጐጂ ነው፡፡

ዛላዎች ወጡ

ዛላዎች አደጉ ወይም ተንዠረገጉ

Genesis 41:7

የቀጨጩ የእሸት ወይም የእህል ዛላዎች

እህል የተባለው ቃል የታወቀ ነው:: አት “የቀጨጩ የእህል ዛላዎች” (የተደበቁ ቃላትን የመግልጽ ዘይቤ ይመልከቱ)

ዋጡአቸው

በሉአቸው ሰው ምግብን እንደሚበላ የቀጨጩ የእሸት ዛላዎች ጤናማ የእሸት ዛላዎች ሲውጡ ፈርዖን በሕልሙ አየ

ሙሉና ፍሬያቸው የተንዠረገገውን የእሸት ዛላዎች

ጤናማና መልካም የእሸት ዛላዎች

በዘፍጥረት 41:5 የዚህ ተመሣሣይ ሀረግ እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ ነቃ

ከእንቅልፉ ነቃ

እነሆ

እዚህ እነሆ የሚለው ቃል ፈርዖ ባየው ነገር እንደተገረመ ያሳያል

ሕልም ነበር

ሕልም ሲያልም ነበር

እንዲህም ሆነ

ይህ ሀረግ የተጠቀመው የታሪኩ አድስ ክፍል መጀመሩን ለማመልከት ነው:: በቋንቋዎ ይህን የሚገልጹበት መንገድ ካለ ይጠቀሙ:: (አድስ ክስተት ስለማስታወቅ ይጠቀሙ)

መንፈሱ ታወከበት

እዚህ መንፈሱ የሚለው ቃለ የውስጥ ማንነቱን ወይም ስሜቱን ያመለክታል አት “በውስጥ ማንነቱ ታወከ” ወይም “ታወከ” (ተመሣሣይ ምትክ ቃል ስለመጠቀም ይመልከቱ)

ልኮና አስጠርቶ

አገልጋዮቹን እንደላካቸው መረዳት ይቻላል:: አት “እንዲጠሩ አገልጋዮቹን ላካቸው ወይም አገልጋዮቹ እንደጠሩ አዘዛቸው” (የተደበቁ ቃላትን የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)

የግብጽ አስማተኞችንና ጥበበኞች

የጥንት ነገሥታት አስማተኞችንና ጥበበኞችን እንደአማካሪዎች ይጠቀሙ ነበር

Genesis 41:9

የመጠጥ አሳላፊዎችን አለቃ

ይህ ለንጉሡ መጠጥን የሚያዘጋጅና የሚያቀርብ መሪ ሰው ነበር፡፡ በዘፍጥረት 4ዐ፡2 እነዚህ ቃላት እንዴት እንደተተረጐሙ ይመልከቱ፡

የሠራሁት በደል ዛሬ ታወሰኝ

ዛሬ የሚለው ቃል የተጠቀመው አስንዎት ለመስጠት ነው በደሉ ቀደም ብሎ ለፈርዖን መናገር የነበረበት አንድ ነገር ነገር ግን ያልተናገረበት ነው:: አት “ለአንተ መናገር የረሳሁትን አሁን አስታወስኩ”

ፈረዖን ተቆጥቶ ነበር

የመጠጥ አሳላፊዎች አለቃ ፈርዖንን አንደ ሶሰተኛ ወገን ሰው ያመለክታል ይህም አነስተኛ ኃላፊነት ያለው ከፍተኛ ኃላፊነት ያለው የሚያስቀምጥበት የተለመደ መንገድ ነው እርስዎ ፈርዖን ተቆጥተው ነበር (አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)

ከእርሱ አገልጋዮች ጋር

እዚህ እርሱ ፈርዖንን ያመለክታል አገልጋዮች የመጠጥ አሳላፊዎች አለቃና የእንጀራ ቤት አዛዥ ያመለክታል:: አት “እኛ አገልጋዮችህ” (አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)

እኔንና የእንጀራ ቤት አዛዡን በዘበኞች አለቃ ግቢ አስሮን ነበር

እኔንና የእንጀራ ቤት አዛዡን በዘበኞች አለቃ ኃላፊነት በተሰጠው እስር ቤት እስሮን ነበር:: እዚህ “ቤት” እስር ቤትን ያመለክታል::

የዘበኞች አለቃ

ንጉሡ ጠባቂዎች ላይ ኃላፊነት የተሰጠው ወታደር ነው በዘፍጥረት 2ዐ:2-3 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ::

የእንጀራ ቤት አዛዥ

ለንጉሡ ምንብን የሚያዘጋጅ ዋና አስፈላጊ ሰው ነው፡፡ በዘፍጥረት 2ዐ:2-3 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ::

እርሱና እኔ በአንዲት ሌሊት ሕልም አየን

“እኛ ሁለታችን በአንድ ሌሊት ሕልም አለምን” እዚህ እኛ የመጠጥ አሳላፊዎች አለቃንና እንጀራ ቤት አዛዡን ያመለክታል (ነጠላና ብዙ እኛ ይመልከቱ)

የእያንዳንዳችን ሕልም የራሱ የሆነ ትርጉም ነበረው

ሕልሞቻችን የተለያየ ትርጉም ነበራቸው

Genesis 41:12

አጠቃላይ መረጃ

የመጠጥ አሳላፊዎች አለቃ ለፈርዖ መናገሩን ቀጠለ

ከእኛ ጋር ነበር

በእስር ቤት ከእንጀራ ቤት አዛዥና ከእኔ ጋር ነበር

የዘበኞች አለቃ

ንጉሡ ጠባቂዎች ላይ ኃላፊነት የተሰጠው ወታደር ነው በዘፍጥረት 2ዐ:2-3 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ::

ሕልሞቻችንን በነገርነው ጊዜ ፊቺውን ነገረን

ሕልሞቻችንን ነገርነው እናም እርሱ ትርጉምቻቸውን ነገረን

ለእያንዳንዳችን እንደሕልማችን ተረጐመልን

እዚህ እርሱ ወይም እያንዳንዱ የሕልሙ ተርጓሚውን ሳይሆን የመጠጥ አሳላፊዎች አለቃንና የእንጀራ ቤት አዛዥ በግል የሚያመለክት ነው አት ለእያንዳንዳችን ምን ሊሆን እንዳለ አስረዳን (አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ወገን ሰው አጠቃቀም ይመልከቱ)

በዚያን ጊዜ

ይህ ሀረግ የተጠቀመው በታሪኩ አስፈላጊ ክስተት ለማመልከት ነው በቋንቋዎ ይህን መግለጽ የሚችሉበት መንገድ ካለ ይጠቀሙ

እርሱ እንደተረጐመልን ሆነ

ስለሕልሞቻችን እንደነገረን ሆነ

ፈርዖን ወደ ሹሜቴ መለሰኝ

እዚህ የመጠጥ አሳላፊዎች አለቃ ማከበሩን ለመግለጽ የፈርዖን የማዕረግ ስም ይጠቀማል:: አት ወደ ሥራዬ እንዲመለስ ፈቀድክልኝ (አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)

እርሱን ወይም ሌላኛውን

የእንጀራ ቤት አዛዡን

እርሱ ሰቀለው

እዚህ እርሱ ፈርዖንን ያመለክታል እና ይህም የእንጀራ ቤት አዛዡን እንዲሰቅሉት ፈርዖን ወታደሮቹን ማዘዙን ይወክላል አት እንዲሰቀል እርስዎ ወታደረችዎን አዝዘዋል:: (አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽና ተዛማጅ ምትክ ቃላትን ስለመጠቀም ዘይቤ ይመልከቱ

Genesis 41:14

ፈርዖንም ሊኮ አስጠራ

ፈርዖን አገልጋዮቹን እንደላከ ይታወቃል አት ዮሴፍን እንዲያመጡት አገልጋዮችን ላከ (የተደበቁ ቃሎችን የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)

ከግዞት ቤት

“ከእስር ቤት” ወይም “ከወህኒ”

ጸጉሩን ከተላጨ

በፈርዖን ፊት ለመቅረብ በመዘጋጀት ጊዜ የፊትና የራስ ጸጉርን መላጨት የተለመደ ተግባር ነበር

ፈርዖን ፊት መጣ

እዚህ መጣ የሚለው ገባ በሚለው ሊገለጽ ይችላል አት ፈርዖን ፊት ገባ (መጣ እና ገባ ይመልከቱ)

የሚተረጉመውም አልተገኘም

ሊተረጉምልኝ የቻለ አንድም ሰው አልተገኘም

አንተ የመተርጐም ችሎታ አለህ

አንተ ትርጉሙን ሊትነግረኝ ትችላለህ

ይህ በእኔ አይደለም

እኔ የመተርጐም ችሎታ የለኝም

እግዚአብሔር በደኀንነት ለፈርዖን ይመልስለታል

እግዚአብሔር ለፈርዖን የሚሻውን ትርጉም ይሰጠዋል

Genesis 41:17

እነሆ ቆሜ ነበር

ስለሚያስገርመው መረጃ ዮሴፍ ትኩረት እንዲሰጠው ፈርዖን “እነሆ” የሚለውን ቃል ይጠቀማል

በዐባይ ወንዝ ዳር

በዐባይ ወንዝ ዳርቻ የለውን ከፍታ የለውን መሬት ያመለክታል:: በዘፍጥረት 41:3 የዚህ ተመሣሣይ ሀረግ እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ:: አት “በዐባይ ወንዝ ዳር”

እነሆ ሰባት ላሞች

ስለሚያስገርመው መረጃ ዮሴፍ ትኩረት እንዲሰጠው ፈርዖን “እነሆ” የሚለውን ቃል ይጠቀማል

የወፈሩና ያማሩ

“የተቀለቡ/የደለቡና ጤናማ” በዘፍጥረት 41:2 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ::

በቀጠማዎች ውስጥ ወይም በመስኩ ይሰማሩ ነበር

በወንዙም ዳር ያለውን ሣር ይመገቡ ነበር:: በዘፍጥረት 41:2 የዚህ ተመሣሣይ ሀረግ እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ፡፡

Genesis 41:19

እነሆ ሰባት ሌሎች ላሞች

ስለሚያስገርመው መረጃ ዮሴፍ ትኩረት እንዲሰጠው ፈርዖን “እነሆ” የሚለውን ቃል ይጠቀማል

የከፉና የከሱ

አቅሜ ደካሞችና የከሱ ወይም የቀጨጩ በዘፍጥረት 41:3 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ

እንደዚህ የሚያስከፉ

“አስከፊ” የሚለው ረቂቅ ስም እንደ ቅጽል ሊተረጐም ይችላል:: አት “የሚያስከፉ ላሞች” ወይም “የማይጠቅሙ የሚመስሉ ላሞች” (ረቂቅ ስሞች ይመልከቱ)

የወፈሩ ላሞች

“የደለቡ ወይም የተቀለቡ ላሞች” በዘፍጥረት 41:2 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ::

እንደዋጧቸው ምንም ሊታወቅ አይችልም ነበር

ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “የከሱ ላሞች የወፈሩትን መዋጣቸውን ማንም ሊነግረው እስከማይችል ነበር:: (ተሻጋሪ ግሥና የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)

Genesis 41:22

አጠቃላይ መረጃ

ፈርዖን ሕልሙን ለዮሴፍ መናገሩን ቀጠለ

በሕልሜ አየሁ

ይህ ፈርዖን ከነቃና ተመልሶ ከተኛ በኋላ ያየውን ሕልም ይጀምራል፡፡ አት “እንደገናም ሕልም አለምሁ” (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)

እነሆ ሰባት የእሸት ዛላዎች

ስለሚያስገርመው መረጃ ዮሴፍ ትኩረት እንዲሰጠው ፈርዖን “እነሆ” የሚለውን ቃል ይጠቀማል::

ሰባት የእሸት ዛላዎች

የእሸት ወይም የእህል የሚለው አባባል የታወቀ ነው:: አት “ሰባት የእህል ዛላዎች” (ምትክ ቃላት የመጠቀም ዘይቤ ይመልከቱ)

በአንድ አገዳ ሲወጡ

“በአንድ አገዳ ሲንዠረግጉ” አገዳ ወፍራምና ረጅም የተክል አካል ነው:: በዘፍጥረት 41:5 ይህን ሀረግ እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ::

እነሆ ሰባት ሌሎች የእሸት ዛላዎች

ስለሚያስገርመው መረጃ ዮሴፍ ትኩረት እንዲሰጠው ፈርዖን “እነሆ” የሚለውን ቃል ይጠቀማል::

የጠወለጉ

የደረቁና ፍሬ አልባ የሆኑ

በምሥራቅ ነፋስ

“ከበረሃማ ቦታ የሚነፍሰው የምሥራቅ ንፋስ” የምሥራቁ ንፋስ ሙቄት አብዛኛውን ጊዜ ለእህሎች እጅግ አደገኛ ነበር::

ተንዠረገገ

አደገ ወይም ፍሬ ሰጠ

የቀጨጩ የእሸት ወይም የእህል ዛላዎች

የእህል የሚለው ቃል የታወቀ ነው በዘፍጥረት 41:7 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ አት የቀጨጩ የእህል ዛላዎች (የተደበቁ ቃላትን የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)

ዋጧቸው

“በሉ” ፈርዖን ያለመው ሕልም ሰው ምግብን እንደሚበላ ጤናማ ያልሆኑ የበቆሎ እህሎች ጤናማ ያልሆኑትን እንደበሉ ነው:: በዘፍጥረት 41:7 የዚህ ተመሣሣይ ሀረግ እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ::

የሚችል ማንም አልተገኘም

የሚችል አንድም አልተገኘም ወይም ማንም አልቻለም

Genesis 41:25

የፈርዖን ሕልሞች ተመሣሣይ ናቸው

ትርጉሞችም ተመሣሣይ ናቸው የሚል አንድምታ አለው:: አት “ሁለቱም ሕልሞች ተመሳሳይ ትርጉም አላቸው” (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)

እግዚአብሔር ሊያደርግ ያለውን ለፈርዖን አስታወቀው

ዮሴፍ ፈርዖንን እንደሳስተኛ ወገን ሰው ያናግረዋል ይህ አክብሮትን መግለጫ መንገድ ነው:: እንደ ሁለተኛ ወገን ሰው መግለጽ ይቻላል:: አት “ቶሎ ሊያደርግ ያለውን እያሳየህ ነው” (አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)

Genesis 41:27

አጠቃላይ መረጃ

ዮሴፍ የፈርዖንን ሕልም መተርጐም ይቀጥላል፡፡

የከሱና አስከፊ መልክ ያላቸው ላሞች

የቀጨጩና ዐቅሜ ደካማ ላሞች በዘፍጥረት 41:3 የዚህ ተመሳሳይ ሀረግ እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ

በምሥራቅ ነፋስ የተመቱ ሰባት የቀጨጩ የእሸት ዛላዎች

ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “ከምሥራቁ ሙቀት አዘል ነፋስ የተነሣ የቀጨጩ ሰባት የእህል ዛላዎች” (ተሻጋሪ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)

ይህን ለፈርዖን የተናገርኩትን … ለፈርዖን ገልጦለታል

ዮሴፍ ፈርዖንን እንደ ሶስተኛ ወገን ሰው ያናግረዋል ይህም አክብሮች መግለጫ መንገድ ነው:: በሁለተኛ ወገን ሰው መልክ ልገለጽ ይችላል:: “እንደተናገርኩህ እነዚህ ይደረጋሉ…… ፈርዖን ለአንተ ገልጦልሃል” (አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)

እይ ሰባት

“እኔ የሚናገረው እውነትና ጠቃሚ ነውና ትኩረት ስጥ፤ ሰባት”

በመላው የግብጸ ምድር እጅግ የተትረፈረፈ ጥጋብ የሚሆንባቸው ሰባት ዓመታት ይመጣሉ

ጊዜ እንደሚመጣና በወቅቱ በአንድ ቦታ እንደሚሆን ይህ ስለጥጋብ ዓመታት ይናገራል:: አት “የተትረፈረፈ ምግብ በግብጽ በመላው የግብጽ ምድር የሚሆንበት ሰባት ዓመታት ይመጣሉ” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)

Genesis 41:30

አጠቃላይ መረጃ

ዮሴፍ የፈርዖንን ሕልምች መተርጐም ቀጠለ

ከዚህ በኃላ ሰባት የራብ ዓመታት ይሆናሉ

ወደ አንድ ቦታው ተንቀሳቅሶ እንደሚመጣ ነገር ተደርጐ ስለ ሰባት ዓመታት ራስ ተነግሮአል አት ከዚም በኋላ እጅግ ጥቂት ምግብ የሚሆንበት ሰባት ዓመታት ይሆናሉ (ዘይቤይዊ አነጋገር ይመልከቱ)

የራቡ ዘመን አገሪቱን እጅግ ስለሚጐዳት … የጥጋቡ ዘመን ሁለ ጨርሶ አይታወስም::

….የሚመጣው የራብ ዘመን እጅግ ጽኑ ከመሆኑ የተነሣ የጥጋብ ዘመን ፈጽም ይረሳል:: ዮሴፍ ለጉዳዩ አጽንዖት ለመስጠት አንድን ሀሳብ በሁለት መንገድ ይገልጻል (ተመሣሣይ ተጓዳኝ አባባሎችን ይመልከቱ)

በግብጽ ምድር የጥጋብ ዘመን ሁሉ ይረሳል

ምድር ሰዎችን ያመለክታል ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “የግብጽ ሰዎች የተትረፈረፈ ምግብ የነበረበትን ዓመታት ሁሉ ይረሳሉ” (ምትክ ቃላት የመጠቀም ዘይቤና ተሻጋሪ ግሥና የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)

አገሪቱን ይጐዳሉ

አገር የሚለው የአገሪቷን መሬት ሰዎችና መላውን የአገሪቷን አካል ያመለክታል (ምትክ ቃላትን የመጠቀም ዘይቤ ይመልከቱ)

ከሚመጣው ራብ የተነሣ

ይህ ተከትሎ እንደሚመጣ እንደ አንድ ነገር ስለሚመጣው ራብ ወይም ድርቅ ይናገራል፡፡ አት “ከዚያ በኋላ በሚሆነው ራብ ወይም ድርቅ የተነሣ” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)

ሕልሙ ለፈርዖን በሁለት መልክ በድጋሚ መታየቱ ነገሩ ከእግዚአብሔር ዘንድ የተቈረጠ ስለሆነ ነው

ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “እግዚአብሔር ሁለት ሕልሞችን የሰጠህ ነገሮች በእርግጥ እንደሚከሰቱ ለማሣየት ነው” (ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)

Genesis 41:33

አጠቃላይ መረጃ

ዮሴፍ ለፈርዖን መናገሩን ቀጠለ

አሁንም

ይህ በዚህን ጊዜ ማለት አይደለም ነገር ግን ስለሚቀጥለው ጠቃሚ ነጥብ ትኩረት እንዲሰጥበት ነው

እንግዲህ ፈርዖን … ይፈልግ

ዮሴፍ ለፈርዖን እንደ ሶስተኛ ወገን ሰው ይናገራል ይህ አክብሮትን የመግለጫ መንገድ ነው በሁለተኛ ወገን ሰው መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “አንተ ፈርዖን ፈልግ” (አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)

በግብጽ ምድር ላይም ይሹመው

ይሹመው ማለት ኃላፊነት ይስጠው ማለት ነው፡፡ አት “በግብጽ ግዛት ላይ ኃላፊነት ይስጠው ወይም በግብጽ ግዛት ላይ ይሹመው (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)

የግብጽ ምድር

እዚህ ምድር በግብጽ ምድር ያሉ ሰዎችንና ሁሉን ነገር ይወክላል (ተመሣሣይ ተዛማጅ ምትክ ቃላት አጠቃቀም ዘይቤ ይመልቱ)

በግብጽ ምድር ከሚገኘው የእህል ምርት አንድ አምሰተአኛውን ይውሰዱ

አምስተኛ የሚለው ቃል ክፍልፋይ ነው:: የግብጽን ምድር እህል ምርት በአምስት መደብ ይክፈሉ፤ ከዚያም አንዱን እጅ ወይም መደብ ይውሰዱ (ክፍልፋዮችን ይመልከቱ)

በሰባት የጥጋብ ዓመታት

የተትረፈረፈ ምግብ ባለባቸው ሰባት ዓመታት

Genesis 41:35

አጠቃላይ መረጃ

ፈርዖንን መምከሩን ቀጠለ

እነርሱም ይሰብስቡ

ሹማምንት ወይም ኃላፊዎች እንዲሰበስቡ ይደረግ

በእነዚህ በሚመጡት ጥጋብ ዓመታት

እነዚህ ዓመታት አንድ ነገር ተጉዞ ወደ አንድ ቦታ እንደማመጣ እንደሚመጡ ይናገራል:: አት “ቶሎ ሊመጡ ያሉ የጥጋብ ዓመታት” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)

በፈርዖን ሥልጣን ሥር ያከማቹ

በፈርዖን ሥልጣን ሥር የሚለው ሀረግ ፈርዖን ሥልጣን ይስጣቸው ማለት ነው አት እህሉን ለመሰብሰብ የፈርዖንን ሥልጣን ይጠቀም ፈሊጣዊ አነገጋር ይመልከቱ

እነርሱም ይህን ይጠብቁ

እነርሱ የሚለው ቃል እህሉ እንዲጠበቅ የሚያዝዙ ሹማምንቶችንና ወታደሮች ያመለክታል አት ሹማምቶች እህሉ እንዲጠበቅ በዚያው ወታደሮችን ይመድቡ ምትክ ቃላት የመጠቀም ዘይቤ ይመልከቱ

እህሉ ለምድሪቱ ምግብ ይሆናል

ምድሪቱ ሰዎችን ትወክላለች አት እህሉም ለሰዎች ምግብነት ይሆናል (ምትክ ቃላት ስለመጠቀም ይመልከቱ)

በዚህ ሁኔታ ምድሪቱ በራብ አትጠፋም

እዚህ “ምድር” ሰዎችን ይወክላል:: ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል አት “በዚህ መንገድ በራብ ጊዜ ሰዎች አይራቡም” (ምትክ ቃላት አጠቃቀም ዘይቤ ወይም ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)

Genesis 41:37

ይህ ምክር ለፈርዖንና በሎለዎቹ ፊት መልካም ሆነ

ፊት ማየትን የሚያመለክት ሲሆን ማየት ማሰብን ወይም ብያኔን ያመለክታል አት ፈርዖንና ሎሌዎቹ ይህ መልካም እቅድ ሆኖ አገኙት

ሎሌዎች

የፈርዖ ሹማምንት

እንደዚህ ያለ ሰው

ዮሴፍ የገለጸው ዓይነት ሰው

የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት

የእግዚአብሔር መንፈስ የሚኖርበት

Genesis 41:39

እንዳንተ ያለ ብልህ የለም

እንዳንተ ያለ ውሳኔ አቅራቢ የለም:: በዘፍጥረት 41:33 ብልህ እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ::

አንተ የቤተመንግሥቴ የበላይ ትሆናለህ

እዚህ “ቤት” የፈርዖን ቤተመንግሥትና በቤተመንግሥቱ ያሉ ሰዎችን ይወክላል:: የበላይ የሚለው ሀረግ ዮሴፍ የበላይ ኃላፊነት ይሰጠዋል ማለት ነው:: አት በቤተመንግሥቴ በሁሉም ላይ ሥልጣን ይሰጥሃል:: (ምትክ ቃላት ስለመጠቀም ዘይቤና ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)

ሕዝቤ ሁሉ ለሥልጣኔ ይገዛል

ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል በሕዝቤ ላይ ገዥ ትሆናለህና አንተ የሚታዝዘውን ያደርጋሉ:: (ተሻጋሪ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)

በዙፋኔ ብቻ

እዚህ ዙፋን ፈርዖን እንደንጉሥ ገዥ እንደሆነ ይገልጻል:: አት “በንጉሥነት ሚናዬ ብቻ”

እየው አድርጌሃለሁ

“እየው” የሚለው ቃል ፈርዖን በሚቀጥለው ለሚናገረው አጽንዖት ይሰጣል:: አት “እየው አድርጌሃለሁ”

በመላይቱ የግብጽ ምድር ላይ ኃላፊ አድርጌሃለሁ

የበላይ አድርጌሃለሁ ማለት ሥልጣን ሰጥቼሃለሁ ማለት ነው እዚህ ምድር ሰዎችን ያመለክታል አት በግብጽ ምድር ባለው በማንኛውም ላይ ኃላፊነት ሰጥቼሃለሁ (ምትክ ቃል የመጠቀም ዘይቤና ፈሊጣዊ አነጋገር ይጠቀሙ)

Genesis 41:42

ፈርዖንም ባለማኀተሙን ቀለበት አውልቆ …. የወርቅ ሐብል አጠለቀለት

እነዚህ ሁሉ ድርጊቶች የሚያመለክቱት ዮሴፍ ያቀደውን ሁሉ እንዲያደርግ ፈርዖን ለዮሴፍ ሥልጣን መስጠቱን ነው (ምልክታዊ ድርጊት የመልከቱ)

ባለማኀተሙ ቀለበት

ይህ ቀለበት የፈርዖን ማኀተም የተቀረጸበት ነው:: ይህም ያቀደውን እንዲያከናውን ለዮሴፍ ገንዘብና ሥልጣንን ሰጠው::

ከጥሩ የተልባ እግር የተሠራ ልብስ

የተልባ እግር የተሠራ ልብስ ሰማያዊ አበባ ካለው የተልባ እግር የተሠራ ለስላሳ ጠንካራ ልብስ ነው::

የእርሱም በሆነው ሁለተኛው ሠረገላ ላይ አስቀመጠው

ይህ ድርጊት ለሰዎች ግልጽ የሚያደርገው የፈርዖን ሁለተኛ ሰው ዮሴፍ ብቻ መሆኑን ነው (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)

ስገዱ ወይም እጅ ንሡ

ስገዱና ዮሴፍን አክብሩ እጅ መንሣትና መስገድ ክብርንና አክብሮትን የመስጠት ምልክት ነው (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)

ፈርዖን በምድሪቱ ባለው ማንኛውም ላይ ሾመው

ማንኛውም ላይ ሾመው የሚለው ሀረግ ሁሉ ላይ ስልጣን ሰጠው ማለት ነው:: እዚህ ምድር ሰዎችን ያመለክታል በዘፍጥረት 41:41 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ:: አት “በግብጽ ባለው ሁሉ ላይ ሥልጣን ሰጠሁ” (ፈሊጣዊ አነጋገርና ምትክ ቃላት አጠቃቀም ዘይቤ ይመልከቱ)

Genesis 41:44

እኔ ፈርዖን ነኝ … ያለ አንተ

ፈርዖን የራሱን ሥልጣን አጽንቶ ይናገራል፡፡ አት “እንደ ፈርዖን እኔ የማዝዘው ያለአንተ”

ያላንተ ማንም እጁንም እግሩንም አያንሣ

እዚህ “እጅና እግር” የሰዎችን ድርጊቶች ይወክላሉ:: አት “ማንኛውም ሰው ምንም ነገር ያለፈቃድህ በግብጽ አያድርግ ወይም ማንኛውም ሰው ምንም ነገር በግብጽ ከማድረጉ በፊት ያንተን ፈቃድ ይጠይቅ” (ምትክ ቃላት የመጠቀም ዘይቤ ይመልከቱ)

ማንም ሰው

እዚህ “ሰው” ወንድም ሆነ ሴት በአጠቃላይ ማንንም ሰው ያመለክታል:: (በወንድ ጾታ የተገለጹ ቃላት ለሴት ጾታም መሆናቸውን ይመልከቱ)

ጸፍናት ፐዕናህ

ተርጓሚዎች የሚከተውን በግርጌ ማስታወሻ ሊጠቀሱ ይችላሉ:: “ጸፍናት ፐዕናህ” የሚለው ስም “ሚስጢሮችን ገላጭ” ማለት ነው፡፡

የሄልዮቱ ወይም ዖን ከተማ ካህን የጶጥፌራ ልጅ የሚትሆን አስናትን አጋባው

ጶጥፋራ የአስናት አባት ነው:: “ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ”

የሄልዮቱ ካህን

ዖን የጸሐይ አምላክ ራአ አምልዕኮ ማዕከል ያለባትና “የጸሐይ ከተማ” የነበረች እንዲሁም “ሄልዮቱ” ተብላ የሚትጠራ ከተማ ነች (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)

ዮሴፍም በመላይቱ የግብጽ ምድር ተዘዋወረ

ሊመጣ ስላለው ያልታሰበ የድርቅ ጊዜ ዝግጅት ለማድረግ ዮሴፍ በመላይቱ የግሣብ ምድር ተዘዋወረ

Genesis 41:46

ሠላሳ ዓመት ዕድሜ

3ዐ ዓመት ዕድሜ ቁጥሮችን ይመልከቱ

ዮሴፍም በፈርዖን ፊት በቆመ ጊዜ

እዚህ በፊቱ መቆም ዮሴፍ ፈርዖንን ማገልገል መጀመሩን ያሳያል:: አት “ፈርዖንን ማገልገል በጀመረ ጊዜ” (ምትክ ቃላት የመጠቀም ዘይቤ ይመልከቱ)

በመላይቱ የግብጽ ምድር ተዘዋወረ

ዮሴፍ ዕቅዱን ለማከናወን ዝግጅት ሲያደርግ አገሪቱን በጥንቃቄ እንደመረመረ ነው

በሰባቱም የጥጋብ ዓመታት

በሰባቱም መልካም ዓመታት

ምድሪቱ የተትረፈረፈ ሰብል ሰጠች

ምድራቱ ብዙ እህል አመረተች

Genesis 41:48

እርሱም ምርት ሰብስቦ …. አከማቸ

እዚህ “እርሱ” የዮሴፍን አገልጋዮች ያመለክታል:: አት “ዮሴፍ አገልጋዮቹ እንዲሰበስቡ አዘዘ …. አከማቹ (ከፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን እንደ ክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)

ዮሴፍ እንደ ባሕር አሸዋ እጅግ ብዙ እህል አከማቸ

የእህሉን እጅግ መብዛት በአጽንዖት ለመናገር ከባሕር አሸዋ ጋር ያነጻጽራል፡፡ አት “ዮሴፍ ያከማቸው እህል ባህር ዳር እንዳለ አሸዋ እጅግ ብዙ ነበር” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)

ዮሴፍ አከማቸ …. እርሱም አቆመ

እዚህ ዮሴፍ እና እርሱ የዮሴፍን አገልጋዮች ይወክላል:: አት “ዮሴፍ አገልጋዮቹ እንዲያከማቹ አደረገ … እነርሱም አቆሙ” (ከፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን እንደ ክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)

Genesis 41:50

የራብ ዓመታት ከመምጣታቸው በፊት

ሰባቱ የራብ ዓመታት ከመምጣቱ በፊት ይህም አንድ ነገር ተጉዞ ወደ አንድ ቦታ እንደሚመጣ ተደርጐ ስለሚመጡ ዓመታት ይናገራል:: አት “ሰባቱ የራብ ዓመታት ከመጀመራቸው በፊት” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)

አስናት

የአንዲት ሴት ስም ነው:: በዘፍጥረት 41:45 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)

የዖን ካህን

ዖን የጸሐይ አምላክ ራአ አምልዕኮ ማዕከል ያለባትና “የጸሐይ ከተማ” የሆነች እንዲሁም “ሄልዮቱ” ተብላ የሚትጠራ ከተማ ነች፡፡ በዘፍጥረት 41:45 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)

ምናሴ

ተርጓሚዎች የሚከተለውን በግርጌ ማስታወሻ ሊጠቀሙ ይችላሉ:: “ሚናሴ” የሚለው ስም ለመርሳት ምክንያት መሆን ማለት ነው::

የአባቴንም ቤት

ይህ የዮሴፍ አባት ያዕቆብንና ቤተሰቡን ያመለክታል

ኤፍሬም

ተርጓሚዎች የሚከተለውን የግርጌ ማስታወሻ ሊጨምሩ ይችላሉ:: “ኤፍሬም” የሚለው ስም “ፍሬያማ መሆን” ወይም “ልጆችን መውለድ” ማለት ነው::

ፍሬያማ አደረገኝ

“ፍሬያማ” መበልጸግ ወይም ልጆችን መውለድ ማለት ነው:: (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)

በተሠቃየሁበት ምድር

“ሥቃይ” የሚለው ረቂቅ ስም “መከራ ተከበልኩ” በሚለው ሊገለጽ ይችላል:: አት “መከራን በተቀበልሁት ምድር” (ረቂቅ ስሞች ይመልከቱ)

Genesis 41:53

በየአገሩ ሁሉ

ከግብጽ ባለፈ የከነዓንንም ምድር ጨምሮ በዙሪያው ባሉ አገሮች ሁሉ

በመላው የግብጽ ምድር ግን ምግብ ነበር

ይህም የሚያስረዳው በሰባት መልካም ዓመታት ሕዝቡ እህልን እንዲያጠራቅሙ ዮሴፍ ስላዘዛቸው ምግብ ነበራቸው (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)

Genesis 41:55

ራብ በመላው የግብጽ ምድር መስፋፋት ሲጀምር

እዚህ “ምድር” ሰዎችን ይወክላል:: አት “ግብጻዊያን ሁሉ በተራቡ ጊዜ” (ምትክ ቃላት የመጠቀም ዘይቤ ይመልከቱ)

ራቡ በአገሩ ሁሉ ፊት እየተስፋፋ ስለሄደ

እዚህ ፊት የሚለው ቃል ምድር ላይ ማለትን ያመለክታል:: አት “ራቡ በየአገሩ ተስፋፋ” (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)

ዮሴፍ ጐተራዎችን ሁሉ ከፍቶ እህሉ ለግብጻዊያን እንዲሸጥ አደረገ

እዚህ “ዮሴፍ” የዮሴፍን አገልጋዮች ይወክላል:: አት “ዮሴፍ አገልጋዮቹ ጐተራዎችን ሁሉ እንዲከፍቱና ለግብጻዊያን እህል እንዲሸጥ አደረገ” (ክፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን እንደ ክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)

ከምድር ሁሉ ወደ ግብጽ ይመጡ ነበር

እዚህ ምድር ከሁሉ አገራት የሆኑ ሰዎችን ይወክላል:: አት “በዙሪያው ካሉ አገሮች ሁሉ ሰዎች ወደ ግብጽ ይመጡ ነበር” (ምትክ ቃላት የመጠቀም ዘይቤ ይመልከቱ)

በምድር ሁሉ

በመላው ምድር በግብጻዊያንን የንግድ መሥመሮች የሚጠቀሙ በድርቅ የተጠቁ የተለያዩ የንግድ አጋሮችና አገሮች ሁሉ ወደ ግብጽ ይመጡ ነበር እንደማለት ነው