ይህ ሀረግ የታሪኩ አድስ ክፍል መጀመሩን ያመለክታል በቋንቋዎ ይህን የሚገልጹበት መንገድ ካለ ያን ሊጠቀሙ ይችላሉ (አዲስ ክስተትን ማስታወቅ ይመልከቱ)
በእስር ቤት ከዮሴፍ አብረውት ስለነበሩት የፈርዖን መጠጥ አሳላፊዎች አለቃና እንጀራ ቤት አዛዥ ሕልሞችን ዮሴፍ ከተረጐመላቸው ሁለት ዓመታት ካለፊ በኋላ
እዚህ እነሆ የሚለው ቃል በሰፊው ታሪክ ሌላ ክስተት መጀመሩን ያመለክታል በቋንቋዎ ይህን የሚገልጹበት መንገድ ሊኖር ይችላል፡፡ አት “ቆሞ በመገኘቱ ገርሞት ነበር”
ፈርዖ ቆሞ ነበር
ጤናማና የወፈሩ
በወንዙ ዳር የበቀለውን ሣር ይበሉ ነበር
በረግረጋማ ቦታ የሚበቅል ቀጭንና ረጅም ሣር ነው
እዚህ እነሆ የሚለው ቃል ፈረዖን እንደገና ባየው ነገር እንደተገረመ ያሳያል
ታማሚና የከሱ
“በወንዝ ዳር” ወይም “ወንዝ ዳረቻ ላይ” ይህ በአንድ ወንዝ ዳር ጠርዝ የሚገኝ ከፍታ ያለው መሬት ማለት ነው::
“ደካማና የከሱ” በዘፍጥረት 41:3 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ::
“ጤናማና የደለቡ ወይም በደንብ የበሉ” በዘፍጥረት 41:2 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ::
ከእንቅልፉ ነቃ
“ሁለት” የሚለው ቃል ተራ ቁጥር ሁለት ነው:: አት “እንደገና” (ተራ ቁጥሮችን ይመልከቱ)
እዚህ እነሆ የሚለው ቃል ፈርዖን ባየው ነገር እንደተገረመ የሚያሳይ ነው
ዛላዎች ፍሬዎች የሚንዠረግጉበት የበቆሎ ተክል አካል ነው
“በአንድ አገዳ ላይ ያፌራውን ወይም የተንዠረገገውን” አገዳ ወፍራምና ረጅም የተክል ክፍል ነው::
በአንድ አገዳ ጤናማና ያማረ
ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊተረጐም ይችላል:: አት: “ያም ከምሥራቅ ደረቅ አየር የትነሳ የቀጨጩና በዋግ የተመቱ” (ተሻጋሪ ግሥና የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)
የምሥራቅ ንፋስ ከረሃማ ተነሥቶ የሚነፍስ ነው፡፡ የምስራቅ ንፋስ ሙቀት እጅግ ጐጂ ነው፡፡
ዛላዎች አደጉ ወይም ተንዠረገጉ
እህል የተባለው ቃል የታወቀ ነው:: አት “የቀጨጩ የእህል ዛላዎች” (የተደበቁ ቃላትን የመግልጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
በሉአቸው ሰው ምግብን እንደሚበላ የቀጨጩ የእሸት ዛላዎች ጤናማ የእሸት ዛላዎች ሲውጡ ፈርዖን በሕልሙ አየ
ጤናማና መልካም የእሸት ዛላዎች
ከእንቅልፉ ነቃ
እዚህ እነሆ የሚለው ቃል ፈርዖ ባየው ነገር እንደተገረመ ያሳያል
ሕልም ሲያልም ነበር
ይህ ሀረግ የተጠቀመው የታሪኩ አድስ ክፍል መጀመሩን ለማመልከት ነው:: በቋንቋዎ ይህን የሚገልጹበት መንገድ ካለ ይጠቀሙ:: (አድስ ክስተት ስለማስታወቅ ይጠቀሙ)
እዚህ መንፈሱ የሚለው ቃለ የውስጥ ማንነቱን ወይም ስሜቱን ያመለክታል አት “በውስጥ ማንነቱ ታወከ” ወይም “ታወከ” (ተመሣሣይ ምትክ ቃል ስለመጠቀም ይመልከቱ)
አገልጋዮቹን እንደላካቸው መረዳት ይቻላል:: አት “እንዲጠሩ አገልጋዮቹን ላካቸው ወይም አገልጋዮቹ እንደጠሩ አዘዛቸው” (የተደበቁ ቃላትን የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
የጥንት ነገሥታት አስማተኞችንና ጥበበኞችን እንደአማካሪዎች ይጠቀሙ ነበር
ይህ ለንጉሡ መጠጥን የሚያዘጋጅና የሚያቀርብ መሪ ሰው ነበር፡፡ በዘፍጥረት 4ዐ፡2 እነዚህ ቃላት እንዴት እንደተተረጐሙ ይመልከቱ፡
ዛሬ የሚለው ቃል የተጠቀመው አስንዎት ለመስጠት ነው በደሉ ቀደም ብሎ ለፈርዖን መናገር የነበረበት አንድ ነገር ነገር ግን ያልተናገረበት ነው:: አት “ለአንተ መናገር የረሳሁትን አሁን አስታወስኩ”
የመጠጥ አሳላፊዎች አለቃ ፈርዖንን አንደ ሶሰተኛ ወገን ሰው ያመለክታል ይህም አነስተኛ ኃላፊነት ያለው ከፍተኛ ኃላፊነት ያለው የሚያስቀምጥበት የተለመደ መንገድ ነው እርስዎ ፈርዖን ተቆጥተው ነበር (አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)
እዚህ እርሱ ፈርዖንን ያመለክታል አገልጋዮች የመጠጥ አሳላፊዎች አለቃና የእንጀራ ቤት አዛዥ ያመለክታል:: አት “እኛ አገልጋዮችህ” (አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)
እኔንና የእንጀራ ቤት አዛዡን በዘበኞች አለቃ ኃላፊነት በተሰጠው እስር ቤት እስሮን ነበር:: እዚህ “ቤት” እስር ቤትን ያመለክታል::
ንጉሡ ጠባቂዎች ላይ ኃላፊነት የተሰጠው ወታደር ነው በዘፍጥረት 2ዐ:2-3 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ::
ለንጉሡ ምንብን የሚያዘጋጅ ዋና አስፈላጊ ሰው ነው፡፡ በዘፍጥረት 2ዐ:2-3 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ::
“እኛ ሁለታችን በአንድ ሌሊት ሕልም አለምን” እዚህ እኛ የመጠጥ አሳላፊዎች አለቃንና እንጀራ ቤት አዛዡን ያመለክታል (ነጠላና ብዙ እኛ ይመልከቱ)
ሕልሞቻችን የተለያየ ትርጉም ነበራቸው
የመጠጥ አሳላፊዎች አለቃ ለፈርዖ መናገሩን ቀጠለ
በእስር ቤት ከእንጀራ ቤት አዛዥና ከእኔ ጋር ነበር
ንጉሡ ጠባቂዎች ላይ ኃላፊነት የተሰጠው ወታደር ነው በዘፍጥረት 2ዐ:2-3 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ::
ሕልሞቻችንን ነገርነው እናም እርሱ ትርጉምቻቸውን ነገረን
እዚህ እርሱ ወይም እያንዳንዱ የሕልሙ ተርጓሚውን ሳይሆን የመጠጥ አሳላፊዎች አለቃንና የእንጀራ ቤት አዛዥ በግል የሚያመለክት ነው አት ለእያንዳንዳችን ምን ሊሆን እንዳለ አስረዳን (አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ወገን ሰው አጠቃቀም ይመልከቱ)
ይህ ሀረግ የተጠቀመው በታሪኩ አስፈላጊ ክስተት ለማመልከት ነው በቋንቋዎ ይህን መግለጽ የሚችሉበት መንገድ ካለ ይጠቀሙ
ስለሕልሞቻችን እንደነገረን ሆነ
እዚህ የመጠጥ አሳላፊዎች አለቃ ማከበሩን ለመግለጽ የፈርዖን የማዕረግ ስም ይጠቀማል:: አት ወደ ሥራዬ እንዲመለስ ፈቀድክልኝ (አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)
የእንጀራ ቤት አዛዡን
እዚህ እርሱ ፈርዖንን ያመለክታል እና ይህም የእንጀራ ቤት አዛዡን እንዲሰቅሉት ፈርዖን ወታደሮቹን ማዘዙን ይወክላል አት እንዲሰቀል እርስዎ ወታደረችዎን አዝዘዋል:: (አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽና ተዛማጅ ምትክ ቃላትን ስለመጠቀም ዘይቤ ይመልከቱ
ፈርዖን አገልጋዮቹን እንደላከ ይታወቃል አት ዮሴፍን እንዲያመጡት አገልጋዮችን ላከ (የተደበቁ ቃሎችን የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
“ከእስር ቤት” ወይም “ከወህኒ”
በፈርዖን ፊት ለመቅረብ በመዘጋጀት ጊዜ የፊትና የራስ ጸጉርን መላጨት የተለመደ ተግባር ነበር
እዚህ መጣ የሚለው ገባ በሚለው ሊገለጽ ይችላል አት ፈርዖን ፊት ገባ (መጣ እና ገባ ይመልከቱ)
ሊተረጉምልኝ የቻለ አንድም ሰው አልተገኘም
አንተ ትርጉሙን ሊትነግረኝ ትችላለህ
እኔ የመተርጐም ችሎታ የለኝም
እግዚአብሔር ለፈርዖን የሚሻውን ትርጉም ይሰጠዋል
ስለሚያስገርመው መረጃ ዮሴፍ ትኩረት እንዲሰጠው ፈርዖን “እነሆ” የሚለውን ቃል ይጠቀማል
በዐባይ ወንዝ ዳርቻ የለውን ከፍታ የለውን መሬት ያመለክታል:: በዘፍጥረት 41:3 የዚህ ተመሣሣይ ሀረግ እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ:: አት “በዐባይ ወንዝ ዳር”
ስለሚያስገርመው መረጃ ዮሴፍ ትኩረት እንዲሰጠው ፈርዖን “እነሆ” የሚለውን ቃል ይጠቀማል
“የተቀለቡ/የደለቡና ጤናማ” በዘፍጥረት 41:2 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ::
በወንዙም ዳር ያለውን ሣር ይመገቡ ነበር:: በዘፍጥረት 41:2 የዚህ ተመሣሣይ ሀረግ እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ፡፡
ስለሚያስገርመው መረጃ ዮሴፍ ትኩረት እንዲሰጠው ፈርዖን “እነሆ” የሚለውን ቃል ይጠቀማል
አቅሜ ደካሞችና የከሱ ወይም የቀጨጩ በዘፍጥረት 41:3 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ
“አስከፊ” የሚለው ረቂቅ ስም እንደ ቅጽል ሊተረጐም ይችላል:: አት “የሚያስከፉ ላሞች” ወይም “የማይጠቅሙ የሚመስሉ ላሞች” (ረቂቅ ስሞች ይመልከቱ)
“የደለቡ ወይም የተቀለቡ ላሞች” በዘፍጥረት 41:2 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ::
ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “የከሱ ላሞች የወፈሩትን መዋጣቸውን ማንም ሊነግረው እስከማይችል ነበር:: (ተሻጋሪ ግሥና የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)
ፈርዖን ሕልሙን ለዮሴፍ መናገሩን ቀጠለ
ይህ ፈርዖን ከነቃና ተመልሶ ከተኛ በኋላ ያየውን ሕልም ይጀምራል፡፡ አት “እንደገናም ሕልም አለምሁ” (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)
ስለሚያስገርመው መረጃ ዮሴፍ ትኩረት እንዲሰጠው ፈርዖን “እነሆ” የሚለውን ቃል ይጠቀማል::
የእሸት ወይም የእህል የሚለው አባባል የታወቀ ነው:: አት “ሰባት የእህል ዛላዎች” (ምትክ ቃላት የመጠቀም ዘይቤ ይመልከቱ)
“በአንድ አገዳ ሲንዠረግጉ” አገዳ ወፍራምና ረጅም የተክል አካል ነው:: በዘፍጥረት 41:5 ይህን ሀረግ እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ::
ስለሚያስገርመው መረጃ ዮሴፍ ትኩረት እንዲሰጠው ፈርዖን “እነሆ” የሚለውን ቃል ይጠቀማል::
የደረቁና ፍሬ አልባ የሆኑ
“ከበረሃማ ቦታ የሚነፍሰው የምሥራቅ ንፋስ” የምሥራቁ ንፋስ ሙቄት አብዛኛውን ጊዜ ለእህሎች እጅግ አደገኛ ነበር::
አደገ ወይም ፍሬ ሰጠ
የእህል የሚለው ቃል የታወቀ ነው በዘፍጥረት 41:7 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ አት የቀጨጩ የእህል ዛላዎች (የተደበቁ ቃላትን የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
“በሉ” ፈርዖን ያለመው ሕልም ሰው ምግብን እንደሚበላ ጤናማ ያልሆኑ የበቆሎ እህሎች ጤናማ ያልሆኑትን እንደበሉ ነው:: በዘፍጥረት 41:7 የዚህ ተመሣሣይ ሀረግ እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ::
የሚችል አንድም አልተገኘም ወይም ማንም አልቻለም
ትርጉሞችም ተመሣሣይ ናቸው የሚል አንድምታ አለው:: አት “ሁለቱም ሕልሞች ተመሳሳይ ትርጉም አላቸው” (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)
ዮሴፍ ፈርዖንን እንደሳስተኛ ወገን ሰው ያናግረዋል ይህ አክብሮትን መግለጫ መንገድ ነው:: እንደ ሁለተኛ ወገን ሰው መግለጽ ይቻላል:: አት “ቶሎ ሊያደርግ ያለውን እያሳየህ ነው” (አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)
ዮሴፍ የፈርዖንን ሕልም መተርጐም ይቀጥላል፡፡
የቀጨጩና ዐቅሜ ደካማ ላሞች በዘፍጥረት 41:3 የዚህ ተመሳሳይ ሀረግ እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ
ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “ከምሥራቁ ሙቀት አዘል ነፋስ የተነሣ የቀጨጩ ሰባት የእህል ዛላዎች” (ተሻጋሪ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)
ዮሴፍ ፈርዖንን እንደ ሶስተኛ ወገን ሰው ያናግረዋል ይህም አክብሮች መግለጫ መንገድ ነው:: በሁለተኛ ወገን ሰው መልክ ልገለጽ ይችላል:: “እንደተናገርኩህ እነዚህ ይደረጋሉ…… ፈርዖን ለአንተ ገልጦልሃል” (አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)
“እኔ የሚናገረው እውነትና ጠቃሚ ነውና ትኩረት ስጥ፤ ሰባት”
ጊዜ እንደሚመጣና በወቅቱ በአንድ ቦታ እንደሚሆን ይህ ስለጥጋብ ዓመታት ይናገራል:: አት “የተትረፈረፈ ምግብ በግብጽ በመላው የግብጽ ምድር የሚሆንበት ሰባት ዓመታት ይመጣሉ” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ዮሴፍ የፈርዖንን ሕልምች መተርጐም ቀጠለ
ወደ አንድ ቦታው ተንቀሳቅሶ እንደሚመጣ ነገር ተደርጐ ስለ ሰባት ዓመታት ራስ ተነግሮአል አት ከዚም በኋላ እጅግ ጥቂት ምግብ የሚሆንበት ሰባት ዓመታት ይሆናሉ (ዘይቤይዊ አነጋገር ይመልከቱ)
….የሚመጣው የራብ ዘመን እጅግ ጽኑ ከመሆኑ የተነሣ የጥጋብ ዘመን ፈጽም ይረሳል:: ዮሴፍ ለጉዳዩ አጽንዖት ለመስጠት አንድን ሀሳብ በሁለት መንገድ ይገልጻል (ተመሣሣይ ተጓዳኝ አባባሎችን ይመልከቱ)
ምድር ሰዎችን ያመለክታል ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “የግብጽ ሰዎች የተትረፈረፈ ምግብ የነበረበትን ዓመታት ሁሉ ይረሳሉ” (ምትክ ቃላት የመጠቀም ዘይቤና ተሻጋሪ ግሥና የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)
አገር የሚለው የአገሪቷን መሬት ሰዎችና መላውን የአገሪቷን አካል ያመለክታል (ምትክ ቃላትን የመጠቀም ዘይቤ ይመልከቱ)
ይህ ተከትሎ እንደሚመጣ እንደ አንድ ነገር ስለሚመጣው ራብ ወይም ድርቅ ይናገራል፡፡ አት “ከዚያ በኋላ በሚሆነው ራብ ወይም ድርቅ የተነሣ” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “እግዚአብሔር ሁለት ሕልሞችን የሰጠህ ነገሮች በእርግጥ እንደሚከሰቱ ለማሣየት ነው” (ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)
ዮሴፍ ለፈርዖን መናገሩን ቀጠለ
ይህ በዚህን ጊዜ ማለት አይደለም ነገር ግን ስለሚቀጥለው ጠቃሚ ነጥብ ትኩረት እንዲሰጥበት ነው
ዮሴፍ ለፈርዖን እንደ ሶስተኛ ወገን ሰው ይናገራል ይህ አክብሮትን የመግለጫ መንገድ ነው በሁለተኛ ወገን ሰው መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “አንተ ፈርዖን ፈልግ” (አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ወገን ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)
ይሹመው ማለት ኃላፊነት ይስጠው ማለት ነው፡፡ አት “በግብጽ ግዛት ላይ ኃላፊነት ይስጠው ወይም በግብጽ ግዛት ላይ ይሹመው (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)
እዚህ ምድር በግብጽ ምድር ያሉ ሰዎችንና ሁሉን ነገር ይወክላል (ተመሣሣይ ተዛማጅ ምትክ ቃላት አጠቃቀም ዘይቤ ይመልቱ)
አምስተኛ የሚለው ቃል ክፍልፋይ ነው:: የግብጽን ምድር እህል ምርት በአምስት መደብ ይክፈሉ፤ ከዚያም አንዱን እጅ ወይም መደብ ይውሰዱ (ክፍልፋዮችን ይመልከቱ)
የተትረፈረፈ ምግብ ባለባቸው ሰባት ዓመታት
ፈርዖንን መምከሩን ቀጠለ
ሹማምንት ወይም ኃላፊዎች እንዲሰበስቡ ይደረግ
እነዚህ ዓመታት አንድ ነገር ተጉዞ ወደ አንድ ቦታ እንደማመጣ እንደሚመጡ ይናገራል:: አት “ቶሎ ሊመጡ ያሉ የጥጋብ ዓመታት” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
በፈርዖን ሥልጣን ሥር የሚለው ሀረግ ፈርዖን ሥልጣን ይስጣቸው ማለት ነው አት እህሉን ለመሰብሰብ የፈርዖንን ሥልጣን ይጠቀም ፈሊጣዊ አነገጋር ይመልከቱ
እነርሱ የሚለው ቃል እህሉ እንዲጠበቅ የሚያዝዙ ሹማምንቶችንና ወታደሮች ያመለክታል አት ሹማምቶች እህሉ እንዲጠበቅ በዚያው ወታደሮችን ይመድቡ ምትክ ቃላት የመጠቀም ዘይቤ ይመልከቱ
ምድሪቱ ሰዎችን ትወክላለች አት እህሉም ለሰዎች ምግብነት ይሆናል (ምትክ ቃላት ስለመጠቀም ይመልከቱ)
እዚህ “ምድር” ሰዎችን ይወክላል:: ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል አት “በዚህ መንገድ በራብ ጊዜ ሰዎች አይራቡም” (ምትክ ቃላት አጠቃቀም ዘይቤ ወይም ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)
ፊት ማየትን የሚያመለክት ሲሆን ማየት ማሰብን ወይም ብያኔን ያመለክታል አት ፈርዖንና ሎሌዎቹ ይህ መልካም እቅድ ሆኖ አገኙት
የፈርዖ ሹማምንት
ዮሴፍ የገለጸው ዓይነት ሰው
የእግዚአብሔር መንፈስ የሚኖርበት
እንዳንተ ያለ ውሳኔ አቅራቢ የለም:: በዘፍጥረት 41:33 ብልህ እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ::
እዚህ “ቤት” የፈርዖን ቤተመንግሥትና በቤተመንግሥቱ ያሉ ሰዎችን ይወክላል:: የበላይ የሚለው ሀረግ ዮሴፍ የበላይ ኃላፊነት ይሰጠዋል ማለት ነው:: አት በቤተመንግሥቴ በሁሉም ላይ ሥልጣን ይሰጥሃል:: (ምትክ ቃላት ስለመጠቀም ዘይቤና ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል በሕዝቤ ላይ ገዥ ትሆናለህና አንተ የሚታዝዘውን ያደርጋሉ:: (ተሻጋሪ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)
እዚህ ዙፋን ፈርዖን እንደንጉሥ ገዥ እንደሆነ ይገልጻል:: አት “በንጉሥነት ሚናዬ ብቻ”
“እየው” የሚለው ቃል ፈርዖን በሚቀጥለው ለሚናገረው አጽንዖት ይሰጣል:: አት “እየው አድርጌሃለሁ”
የበላይ አድርጌሃለሁ ማለት ሥልጣን ሰጥቼሃለሁ ማለት ነው እዚህ ምድር ሰዎችን ያመለክታል አት በግብጽ ምድር ባለው በማንኛውም ላይ ኃላፊነት ሰጥቼሃለሁ (ምትክ ቃል የመጠቀም ዘይቤና ፈሊጣዊ አነጋገር ይጠቀሙ)
እነዚህ ሁሉ ድርጊቶች የሚያመለክቱት ዮሴፍ ያቀደውን ሁሉ እንዲያደርግ ፈርዖን ለዮሴፍ ሥልጣን መስጠቱን ነው (ምልክታዊ ድርጊት የመልከቱ)
ይህ ቀለበት የፈርዖን ማኀተም የተቀረጸበት ነው:: ይህም ያቀደውን እንዲያከናውን ለዮሴፍ ገንዘብና ሥልጣንን ሰጠው::
የተልባ እግር የተሠራ ልብስ ሰማያዊ አበባ ካለው የተልባ እግር የተሠራ ለስላሳ ጠንካራ ልብስ ነው::
ይህ ድርጊት ለሰዎች ግልጽ የሚያደርገው የፈርዖን ሁለተኛ ሰው ዮሴፍ ብቻ መሆኑን ነው (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)
ስገዱና ዮሴፍን አክብሩ እጅ መንሣትና መስገድ ክብርንና አክብሮትን የመስጠት ምልክት ነው (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)
ማንኛውም ላይ ሾመው የሚለው ሀረግ ሁሉ ላይ ስልጣን ሰጠው ማለት ነው:: እዚህ ምድር ሰዎችን ያመለክታል በዘፍጥረት 41:41 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ:: አት “በግብጽ ባለው ሁሉ ላይ ሥልጣን ሰጠሁ” (ፈሊጣዊ አነጋገርና ምትክ ቃላት አጠቃቀም ዘይቤ ይመልከቱ)
ፈርዖን የራሱን ሥልጣን አጽንቶ ይናገራል፡፡ አት “እንደ ፈርዖን እኔ የማዝዘው ያለአንተ”
እዚህ “እጅና እግር” የሰዎችን ድርጊቶች ይወክላሉ:: አት “ማንኛውም ሰው ምንም ነገር ያለፈቃድህ በግብጽ አያድርግ ወይም ማንኛውም ሰው ምንም ነገር በግብጽ ከማድረጉ በፊት ያንተን ፈቃድ ይጠይቅ” (ምትክ ቃላት የመጠቀም ዘይቤ ይመልከቱ)
እዚህ “ሰው” ወንድም ሆነ ሴት በአጠቃላይ ማንንም ሰው ያመለክታል:: (በወንድ ጾታ የተገለጹ ቃላት ለሴት ጾታም መሆናቸውን ይመልከቱ)
ተርጓሚዎች የሚከተውን በግርጌ ማስታወሻ ሊጠቀሱ ይችላሉ:: “ጸፍናት ፐዕናህ” የሚለው ስም “ሚስጢሮችን ገላጭ” ማለት ነው፡፡
ጶጥፋራ የአስናት አባት ነው:: “ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ”
ዖን የጸሐይ አምላክ ራአ አምልዕኮ ማዕከል ያለባትና “የጸሐይ ከተማ” የነበረች እንዲሁም “ሄልዮቱ” ተብላ የሚትጠራ ከተማ ነች (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)
ሊመጣ ስላለው ያልታሰበ የድርቅ ጊዜ ዝግጅት ለማድረግ ዮሴፍ በመላይቱ የግሣብ ምድር ተዘዋወረ
3ዐ ዓመት ዕድሜ ቁጥሮችን ይመልከቱ
እዚህ በፊቱ መቆም ዮሴፍ ፈርዖንን ማገልገል መጀመሩን ያሳያል:: አት “ፈርዖንን ማገልገል በጀመረ ጊዜ” (ምትክ ቃላት የመጠቀም ዘይቤ ይመልከቱ)
ዮሴፍ ዕቅዱን ለማከናወን ዝግጅት ሲያደርግ አገሪቱን በጥንቃቄ እንደመረመረ ነው
በሰባቱም መልካም ዓመታት
ምድራቱ ብዙ እህል አመረተች
እዚህ “እርሱ” የዮሴፍን አገልጋዮች ያመለክታል:: አት “ዮሴፍ አገልጋዮቹ እንዲሰበስቡ አዘዘ …. አከማቹ (ከፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን እንደ ክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
የእህሉን እጅግ መብዛት በአጽንዖት ለመናገር ከባሕር አሸዋ ጋር ያነጻጽራል፡፡ አት “ዮሴፍ ያከማቸው እህል ባህር ዳር እንዳለ አሸዋ እጅግ ብዙ ነበር” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
እዚህ ዮሴፍ እና እርሱ የዮሴፍን አገልጋዮች ይወክላል:: አት “ዮሴፍ አገልጋዮቹ እንዲያከማቹ አደረገ … እነርሱም አቆሙ” (ከፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን እንደ ክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
ሰባቱ የራብ ዓመታት ከመምጣቱ በፊት ይህም አንድ ነገር ተጉዞ ወደ አንድ ቦታ እንደሚመጣ ተደርጐ ስለሚመጡ ዓመታት ይናገራል:: አት “ሰባቱ የራብ ዓመታት ከመጀመራቸው በፊት” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
የአንዲት ሴት ስም ነው:: በዘፍጥረት 41:45 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)
ዖን የጸሐይ አምላክ ራአ አምልዕኮ ማዕከል ያለባትና “የጸሐይ ከተማ” የሆነች እንዲሁም “ሄልዮቱ” ተብላ የሚትጠራ ከተማ ነች፡፡ በዘፍጥረት 41:45 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)
ተርጓሚዎች የሚከተለውን በግርጌ ማስታወሻ ሊጠቀሙ ይችላሉ:: “ሚናሴ” የሚለው ስም ለመርሳት ምክንያት መሆን ማለት ነው::
ይህ የዮሴፍ አባት ያዕቆብንና ቤተሰቡን ያመለክታል
ተርጓሚዎች የሚከተለውን የግርጌ ማስታወሻ ሊጨምሩ ይችላሉ:: “ኤፍሬም” የሚለው ስም “ፍሬያማ መሆን” ወይም “ልጆችን መውለድ” ማለት ነው::
“ፍሬያማ” መበልጸግ ወይም ልጆችን መውለድ ማለት ነው:: (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)
“ሥቃይ” የሚለው ረቂቅ ስም “መከራ ተከበልኩ” በሚለው ሊገለጽ ይችላል:: አት “መከራን በተቀበልሁት ምድር” (ረቂቅ ስሞች ይመልከቱ)
ከግብጽ ባለፈ የከነዓንንም ምድር ጨምሮ በዙሪያው ባሉ አገሮች ሁሉ
ይህም የሚያስረዳው በሰባት መልካም ዓመታት ሕዝቡ እህልን እንዲያጠራቅሙ ዮሴፍ ስላዘዛቸው ምግብ ነበራቸው (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)
እዚህ “ምድር” ሰዎችን ይወክላል:: አት “ግብጻዊያን ሁሉ በተራቡ ጊዜ” (ምትክ ቃላት የመጠቀም ዘይቤ ይመልከቱ)
እዚህ ፊት የሚለው ቃል ምድር ላይ ማለትን ያመለክታል:: አት “ራቡ በየአገሩ ተስፋፋ” (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)
እዚህ “ዮሴፍ” የዮሴፍን አገልጋዮች ይወክላል:: አት “ዮሴፍ አገልጋዮቹ ጐተራዎችን ሁሉ እንዲከፍቱና ለግብጻዊያን እህል እንዲሸጥ አደረገ” (ክፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን እንደ ክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
እዚህ ምድር ከሁሉ አገራት የሆኑ ሰዎችን ይወክላል:: አት “በዙሪያው ካሉ አገሮች ሁሉ ሰዎች ወደ ግብጽ ይመጡ ነበር” (ምትክ ቃላት የመጠቀም ዘይቤ ይመልከቱ)
በመላው ምድር በግብጻዊያንን የንግድ መሥመሮች የሚጠቀሙ በድርቅ የተጠቁ የተለያዩ የንግድ አጋሮችና አገሮች ሁሉ ወደ ግብጽ ይመጡ ነበር እንደማለት ነው