Genesis 39

Genesis 39:1

ዮሴፍ ወደ ግብጽ ወርዶ ነበር

ወደ ግብጽ መጓዝ ወደ ላይ ወደ ተስፋይቱ ምድር የመጓዝ ተጻራሪ ወደ ታች መውረድ ተደርጐ ይቆጠራል ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መንገድ ሊገለጽ ይችላል:: አት “እስማኤላዊያን ዮሴፍን ወደ ግብጽ ወሰዱት” (ፈሊጣዊ አነጋገርና ተሻጋሪ ግሥ እና የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)

እግዚአብሔር የዮሴፍ ጋር ነበረ

ይህ እግዚአብሔር ዮሴፍን ረድቶታል ሁልጊዜም ከእርሱ ጋር ነበር ማለት ነው:: አት “እግዚአብሔር ዮሴፍን መራው አገዘውም” (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)

አሳዳሪው ቤት ኖረ

እዚህ ጸሓፊው በአሳዳሪው ቤት መሥራቱን በአሳዳሪው ቤት እንደመኖር ይናገራል:: በአሳዳሪዎቻቸው ቤት መሥራት የሚችሉት በጣም ታማኝ የሆኑ ሎሌዎች ብቻ ናቸው፡፡ አት እርሱም በቤት ውስጥ ይሠራ ነበር (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)

Genesis 39:3

አሳዳሪው እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር እንዳለ አየ

አሳዳሪው እግዚአብሔር እርሱን እየረዳ እንደሆነ አየ ማለት ነው አት እግዚአብሔር እየረዳው እንደሆነ አሳዳሪው አየ (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)

እግዚአብሔር ሥራውን ሁሉ እንዳከናወነለት

እግዚአብሔር ዮሴፍ የሚሠራው ሁሉ መከናወንለት አደረገ

ዮሴፍ በእርሱ ዘንድ ሞገስ አገኘ

ሞገስ ማግኘት በአንድ ሰው ተቀባይነትን ማስረገጥ ማለት ነው በእርሱ ዘንድ የሚለው ፈሊጣዊ አባባል በሰውዬው አመለካከት እንደሆነ ያመለክታል:: ተገቢ ትርጉሞች እነሆ 1) ጲጥፋራ በዮሴፍ ተደስቶአል 2) እግዚአብሔር በዮሴፍ ተደስቶአል (ፈሊጣዊ አባባል ይመልከቱ)

ጲጥፋራን አገለገለ

የጲጥፋራ የግል ሎሌው ነበር ማለት ነው

ጲጥፋራ ዮሴፍን በቤቱ ላይ ሾመው ያለውን ሀብት ሁሉ በኃላፊነት ሰጠው

ጲጥፋራ በቤቱና የጲጥፋራ በሆነው ሁሉ ላይ ለዮሴፍ በኃላፊነት ሰጠው

በእርሱ ኃላፊነት ሥር አደረገ

አንድ ነገር በአንድ ሰው ኃላፊነት ሥር ሲሆን ያ ሰው ያንን ነገር ለመንከባከብና ደኀንነቱን ለመጠበቅ ኃላፊነት አለው ማለት ነው:: አት “ዮሴፍ እንዲንከባከብ ሰጠው” (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)

Genesis 39:5

ዮሴፍ በጲጥፋራ ቤትና ባለው ሀብት ሁሉ ላይ ከተሾመበት ጊዜ ጀምሮ እግዚአብሔር የግብጻዊውን ቤት ባረከ

ተውላጤ ስሞችን ከመጠቀምዎ በፊት “ዮሴፍ” እና “ግብጻዊው” የሚሉ ቃላትን መጠቀም ይችላሉ:: ግብጻዊው ዮሴፍን በቤቱና ባለው ሀብት ሁሉ ላይ ኃላፊነት ሰጠው እናም ከጊዜ ወደ ጊዜ በዮሴፍ ምክንያት እግዚአብሔር የግብጻዊውን ቤት ባረከ::

እንዲህም ሆነ

እነዚህ ሁለቱ ጥቅሶች ለሚቀጥለው ክስተት ዳራ መረጃ እንደሆኑ ለአንባቢያን ለመናገር ይህ ሀረግ ተጠቅሞአል

እርሱም እርሱን በቤቱና ባለው ሀብት ሁሉ ላይ ሾመው

ጲጥፋራ ዮሴፍን በቤቱና ባለው ተብት ሁሉ ላይ ሾመው

ባረከው

በሚባረከው ነገር ወይም ሰው መልካም ወይም ጠቃሚ ነገር እንዲደረግ ምክንያት መሆን ማለት ነው

የእግዚአብሔር በረከት ሆነ

እዚህ ጸሐፊው እግዚአብሔር የሰጠውን በረከት በአንድ ነገር ላይ እንደተቀመጠ መሸፈኛ አድርጐ ይናገራል:: አት: “እግዚአብሔር ባረከ” ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ

በግቢም በውጭም ባለው የጲጥፋራ ሀብት ንብረት ሁሉ

ይህ ቤት እረሻውንና ከብቶችን ያለመክታል የዚህ ሙሉ ትርጉም ግልጽ ሊደረግ ይችላል:: አት “በጲጥፋራ ቤትና በከብቶችና እርሻው ሁሉ” (ግምታዊ እውቀትና ጥልቀ መረጃ ይመልከቱ)

ጲጥፋራ ማንኛውንም ጉዳይ በዮሴፍ ቁጥጥር ሥር አድርጐ/በዮሴፍ ላይ ጥሎ ነበር

አንድ ነገር በአንድ ሰው ቁጥጥር ሥር ሲሆን ያ ሰው ሊጠብቀውና ሊንከባከበው ኃላፊነት አለው ማለት ነው አት: “ስለዚህ ጲጥፋራ ባለው ሁሉ ላይ ለዮሴፍ ስልጣን ሰጠው”

ከሚበላው እንጀራ በቀም ምንም የሚያውቀው አልነበረም

ምን ምግብ መመገብ እንዳለበት ከመወሰን በቀር በቤቱ ስላለው ማንኛውም ነገር አይጨነቅም ነበር ይህ በአዎንታዊ መንገድ ሊገለጽ ይችላል አት ጲጥፋራ ምን መመገብ እንደሚፈልግ ብቻ ማሰብ ነበረበት በቤቱ ስላለው ማንኛውም ነገር መጨነቅ የለበትም (ግምታዊ እውቀትና ጥልቀ መረጃ ይመልከቱ)

አሁንም

“አሁንም” የሚለው ቃል ስለ ዮሴፍ ዳራ መረጃ ለመስጠት በታሪኩ መስመር ውስጥ ጣልቃ ማስገባቱን ያመለክታል (ዳራ መረጃ ይመልከቱ)

ዮሴፍ መልከ መልካምና ውብ ነበር

ሁለቱም ቃላት ተመሣሣይ ትርጉም አላቸው ዮሴፍ የሚያስደስት ቁመና እንዳለው ያመለክታሉ:: ጠንካራና ጥሩ ቁመና ነበረው:: አት: “ጠንካራና መልከመልካም ነበር”

Genesis 39:7

ከዚህ በኋላ እንደዚህ ሆነ

እናም ደግሞ ይህ ሀረግ አድስ ክስተት መጀመሩን ሊያመለክት ተጠቅሞአል (አዲስ ክስተት ማታወቅ ይመልከቱ)

እይው

ስሚው ዮሴፍ የጲጥፋራን ሚስት መስብ/ትኩረት ለማግኘት ይህን ቃል ተጠቅሞአል

ጌታዬ በቤቱ ውስጥ ስላለው ሁሉ ምንም የሚያውቀው ነገር የለም

“ጌታዬ በኃላፊነቴ ሥር ስላለው ስለቤቱ ሁሉ ምንም የሚያውቀው ነገር የለም”:: ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “ጌታዬ ስለቤቱ ያምነኛል” (ድርብ አሉታዊነት ይመልከቱ)

ጌታዬ ያለውን ሁሉ በኃላፊነት ለእኔ ስለሰጠኝ

አንድ ነገር “በአንድ ሰው ኃላፊነት ሥር” ሲሆን ያ ሰው እንዲንከባከበውና እንዲጠብቀው ኃላፊነት አለው ማለት ነው:: አት፡ “ያለውን ሁሉ በኃላፊነት ስለሰጠኝ” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)

ለዚህ ቤት ከእኔ የሚበልጥ ሰው የለም

እዚህ ጸሓፊው ኃላፊነትን እንደ ትልቅነት ይናገራል አት: “ከማንም ሰው የበለጠ ለዚህ ቤት ኃላፊነት አለኝ” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)

ከአንቺ በቀር ያልሰጠኝ ነገር የለም

ይህ በአዎንታዊ መንገድ ሊገለጽ ይችላል:: አት: “እርሱ ያለሰጠኝ ነገር ቢኖር አንቺን ብቻ ነው” (አሉታዊነትን በአዎንታዊነት የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)

እንዴት ይህን ክፉ ድርጊት ፈጽሜ በእግዚአብሔር ፊት ኃጢአት እሠራለሁ

ዮሴፍ ትኩረት ለመስጠት ጥያቄ ይጠቀማል ይህ በዐረፍተ ነገር መልክ ሊገለጽ ይችላል አት ይህን ክፉ ድርጊት ፈጽሜ በእግዚአብሔር ፊት ኃጢአት አልሠራም (አግናኝ ጥያቄዎችን ይመልከቱ)

Genesis 39:10

በየዕለቱ ለዮሴፍ ትነግረው ነበር

ከእርስዋ ጋር እንዲተኛ በተደጋጋሚ ትጠይቀው ነበር ማለት ነው:: የዚህ ጥቅስ ሙሉ ትርጉሙ ግልጽ ሊደረግ ይችላል:: አት: “ዮሴፍ ከእርስዋ ጋር እንዲተኛ ትጐተጉተው ነበር” (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)

ከእርስዋም ጋር እንዲሆን

እንዲቀርባት

እንዲህም ሆነ

“እንዲሁም ደግሞ” የሚለው ሀረግ በታሪኩ አድስ ክስተት መጀመሩን ለማመልከት ነው (አዲስ ክስተት ስለማታወቅ ይመልከቱ)

ከቤቱ አገልጋዮችም አንድም ሰው

በቤቱ ከሚያገለግሉ ሰዎች ማንም

ሸሽቶ ከቤት ወጣ

“እናም ወዲያው ሮጦ ወደ ውጪ ወጣ” ወይም “እናም ወዲያው ሮጦ ከቤት ወጣ”

Genesis 39:13

እንዲህም ሆነ …. ጠራች

ከዚያም …. ጠራች እንዲህም ሆነ የሚለው ሀረግ በታሪኩ ሁለተኛውን ክስተት ለማመልከት ተጠቅሞአል (አዲስ ክስተት ስለማስታወቅ ይመልከቱ)

ሸሽቶ ወደ ውጭ ወጣ

ወዲያው ሮጦ ከቤት ወጣ

የቤትዋን ሰዎች

በቤትዋ የሚሠሩ ሰዎች

አያችሁ

“ተመልከቱ” ወይም “ሰማችሁ” ወይም “ስለሚናገረው ነገር ትኩረት አድርጉ”

ከእኔ ጋር ሊተኛ ወደ እኔ ገባ

እዚህ የጲጥፋራ ሚስት ዮሴፍ ሊይዛትና ከእርስዋ ጋር ሊተኛ እንደሞከረ ትከሳለች

እንዲህም ሆነ መጮሄን ሲሰማ

ድምጼን ከፍ አድርጌ መጮሄን ሲሰማ እንዲህም ሆነ የሚለው ሀረግ የተጠቀመው በታሪኩ ሁለተኛውን ክስተት ለማመልከት ነው (አዲስ ክስተት ስለማስታወቅ ይመልከቱ)

Genesis 39:16

ጌታውም

የዮሴፍ ጌታ ይህ ጲጥፋራን ያመለክታል::

እንዲህ ስትል ነገረችው

ይህን ነገር እንዲህ ብላ ነገረችው

ወደ እኛ ያመጣሄው

“እኛ” የሚለው ቃል ጲጥፋራን ሚስቱንና ሌሎች በቤት ውስጥ ያሉትን ጠቃልላል (ሁሉ አቀፍ እኛን ይመልከቱ)

መሣለቂያ ሊያደርገኝ ወደ እኔ ገባ

መሣቂያ ሊያደርገኝ ወደ እኔ ገባ መሣለቂያ የሚለው ቃል ሊይዘኝና ከእኔ ጋር ሊተኛ የሚለውን አባባል በንኀብነት ወይም አንድን ነገር ለዘብ ባለ በተዘዋዋሪ መንገድ የሚገለጽ ነው:: አት “ወዳለሁበት ገባ አስገድዶ ከእኔ ጋር ሊተኛ ሞከረ” (ንኀብነት ወይም አንድን ነገር ለዘብ ባለ በተዘዋዋሪ መንገድ የሚገለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)

እንዲህም ሆነ

“ከዚያም” የጲጥፋራ ሚስት ይህን ሀረግ የተጠቀመችው ዮሴፍ ከእርስዋ ጋር ለመተኛት መሞከሩን ለእርሱ የሚትነግረውን የታሪኩን ሁለተኛውን ክስተት ለማመልከት ነው::(አዲስ ክስተት ስለማታወቅ ይመልከቱ)

ሸሽቶ ወደ ውጭ ወጣ

ወዲያው ሮጦ ከቤት ወጣ

Genesis 39:19

እንዲህም ሆነ

“እንዲህም ሆነ” የሚለው ሀረግ በታሪኩ አዲስ ክስተት መጀመሩን ለማመልከት ተጠቅሞአል (አዲስ ክስተት ስለማስታወቅ ይመልከቱ)

ጌታውም

የዮሴፍ ጌታ ይህ ጲጥፋራን ያመለክታል ይህ መረጃ ግልጽ ሊደረግ ይችላል አት የዮሴፍ ጌታ ጲጥፋራ

እጅግ ተቈጣ

ጲጥፋራ እጅግ ተቈጣ

የንጉሡ እስረኞች ወደ ተጋዙበት እስር ቤት

ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል አተ ንጉሡ እስረኞችን ያኖረበት ቦታ ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ

በዚያ ነበረ

ዮሴፍ በዚያ ቆየ

Genesis 39:21

ነገር ግን እግዚአብሔር ከዮሴፍ ጋር ነበረ

እግዚአብሔር ለዮሴፍ ተጠነቀቀለት እናም ቸር ነበረ:: “ነገር ግን እግዚአብሔር ለዮሴፍ ቸር ነበር” ወይም “እግዚአብሔር ዮሴፍን ተንከባከበ” (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)

የቃል ኪዳን ታማኝነቱን ገለጸለት

“ታማኝነት” የሚለው ረቂቅ ስም “ታማኝ” ወይም “በታማኝነት” ሊገለጽ ይችላል:: አት ከእርሱ ጋር ለገባው ቃል ኪዳን ታማኝ ነበር ወይም በታማኝነት ወደደው (ረቂቅ ስሞች ይመልከቱ)

በወህኑ ቤት አዛዡም ዘንድ ሞገስን ሰጠው

ይህም እግዚአብሔር የወህኑ ቤት አዛዥ ዮሴፍን እንዲቀበለውና እንዲንከባከበው አደረገው አት እግዚአብሔር የእስር ቤቱ አዛዥ በዮሴፍ እንዲደሰት አደረገው (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)

የእስር ቤቱ አዛዥ

“የእስረኞች አስተዳደር” ወይም “በእስር ቤቱ ኃላፊነት የተሰጠው”

በዮሴፍ እጅ አሳልፎ ሰጣቸው

እዚህ “እጅ” የሚለው የዮሴፍን ኃይል/አቅም ወይም ታማኝ ኃላፊነት ይወክላል”” አት “ዮሴፍን አለቃ አደረገው” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)

በዚያ ለሚደረገው ማንኛውም ነገር ዮሴፍ ኃላፊ ነበር

“ዮሴፍ በዚያ ለሚደረገው ነገር ሁሉ ኃላፊ ነበር”

እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ስለነበረ

ይህ እግዚአብሔር እንዴት እንደረዳውና እንደመራው የሚያመለክት ነው፡፡ አት “እግዚአብሔር ዮሴፍን ስለመራው” (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)

የሚያደርገውን ሁሉ እግዚአብሔር ያሳካለት ነበር

ዮሴፍ የሚያደርገውን ሁሉ እግዚአብሔር ያሳካለት ነበር