መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን፣ “ለምጽ” የተለያዩ የቆዳ በሽታዎችን ያመለክት ነበር። አንድ ሰው ከእነዚህ የቆዳ በሽታዎች በአንዱ ከተያዘ ርኵስ ተብሎ ይቆጠር ነበር።
“ከብት” የሚለው ሳር የሚበሉ በዋነኛነት ደረጃ ለሚሰቱት ሥጋና ወተት ሰዎች የሚያረቧቸው ባለ አራት እግር የእርሻ እንስሳት ናቸው። እንዲህ ካሉት እንስሳት እንስቷ “ላም” ስትባል፣ ተባዕቱ፣ “ወይፈን” ከእነርሱ የሚወለደው፣ “ጥጃ” ይባላል።
“ላከ” አንድ ሰው ወይም አንድ ነገር ወደ ሌላ ቦታ እንዲሄድ ማድረግ ማለት ነው። አንድን ሰው፣ “መላክ” አንድን ነገር እንዲያደርግ ወይም አንድን ተልዕኮ እንዲፈጽም መናገር ወይም ማዘዝ ማለት ነው
“ሌባ” ወይም፣ “ወንበዴ” ገንዘብ ወይም ንብረት ከሌሎች የሚሰርቅ ሰው ነው። በብዙ ቁጥር ሲሆን፣ “ሌቦች” ይሆናል።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “ልሳን” በርካታ ምሳሌያዊ ትርጕሞች አሉት።
“ልዑል” የሚባለው የንጉሥ ልጅ ነው። ሌሎችን መሪዎች ለማመልከትም ጥቅም ላይ ይውላል። “ልዕልት” የንጉሥ ልጅ ናት።
የአንድ አገር ሴት ገዢ ወይም የንጉሥ ልጅ ልትሆን ትችላለች። ማዳፈን “ማዳፈን” የሚለው ቃል አንድ ነገር ማጥፋት ወይም መርካት የሚፈልግን ነገር ማስቆም ማለት ነው።
ሐሜት ከሰዎች በስተጀርባ ሆነው እነርሱ በተመለከተ የሚናገሩት አፍራሽና አሉታዊ ቃል ነው። ብዙውን ጊዜ በእንዲህ ያለ መልኩ የተነገረው እውነት ሆኖ አይገኝም።
“ሐምራዊ” የሰማያዊና የቀይ ቅልቅል የሆነ ቀለም ስም ነው። ልብስን በዚህ ቀለም ማቅለም በጣም ውድና ሰፊ ጊዜ የሚጠይቅ በመሆኑ ሐምራዊ ልብስ የሀብት፣ የከበሬታና የንጉሣዊነት ምልክት ተደርጎ ይወሰድ ነበር።
ሐሤት በደስታን በፍስሐ መሞላት፣ እጅግ በጣም ደስ መሰኘት ማለት ነው፥
ሐሰተኛ ነብይ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ከእግዚአብሔር ያልተቀበለውን መልእክት ከእግዚአብሔር እንደተቀበለ የሚናገር ሰው ነው።
ሕልም ሰዎች ተኝተው እያለ የሚያዩት ወይም አእምሮአቸው ውስጥ የሚለማመዱት ነገር ነው።
ሕዝብ የሚባለው በአንድ ዐይነት መንግሥታዊ አስተዳደር የሚመራ የሰዎች ስብስብ ነው። ብዙውን ጊዜ በዘር፣ በነገድ፣ በቋንቋና በሌሎችም ባሕርዮች የሚመሳሰሉ ሰዎችን ያካትታል።
ሕጋዊ የሆነ ነገር አሳሪ ከሆነው ደንብ ወይም ሕግ መሠረት የተደረገ ወይም ከእርሱ ጋር የሚስማማ ማለት ነው።
ሕግ ሆን ተብሎ በጽሑፍ የሰፈረና ሥልጣን ባለው አምላክ የሚያስፈጽመው መደበኛ መመሪያ ነው። ሥርዐት (መርሕ) ውሳኔዎችን ለማድረግ መመሪያ ወይም መመዘኛ ነው።
“ዐመፃ” ለማንኛውም ሕግ ወይም ደንብ አለመታዘዝ ማለት ነው። ሕግ አፍራሽነት፣ “ዐመፃ” ሊባል ይችላል።
“መለመን” አንድ ነገር እንዲደረግ ወይም እንዲሰጥ አጥብቆ መጠየቅ ማለት ነው። “ልመና” የሚለው የሚያመለክተው የመለመንን ተግባር ነው።
“መለመን” አንድን ነገር አጥብቆ መጠየቅ ማለት ነው። ብዙውን ጊዜ ገንዘብ ወይም እንጀራ መጠየቅን ይመለከታል።
“መለከት” ሙዚቃ ለመጫወት ወይም ዐዋጅ ለማሰማት ወይም ሕዝብን ለስብሰባ ለመጥራት ጥቅም ላይ የሚውል መሣሪያ ነው።
“መለየት” የሚለው ቃል የሚያመለክተው አንድን ነገር መረዳትን በተለይም ያ ነገር ትክክል ወይም ስሕተት መሆኑን በሚገባ መረዳትን ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በምሳሌያዊ መልኩ ጥቅም ላይ ከዋ፣ “ለበሰ” አንድ ነገር፣ “ተቀዳጀ” ወይም አንድ ነገር ታጠቀ ወይም በአንዳች ሁኔታ ዝግጁ ሆነ ማለት ነው። አንድ ነገር፣ “መልበስ” አንድ ዐይነት ፀባይ ወይም ባሕርይ አዳበረ ማለት ነው።
መልእክተኛ የሚባለው ለሌሎች የሚናገረው ወይም የሚያደርሰው ነገር የተሰጠው ሰው ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት አንዳች ነገር ለማድረግ የሚሰጥ ውል ያለው ተስፋ ቃል ነው። መሐላ የሚያደርግ ሰው የሰጠውን ተስፋ የመፈጸም ግዴታ አለበት።
“መመለስ” ወደ ኋላ መመለስ፣ ወይም አንድን ነገር መልሶ መስጠት ማለት ነው።
መመላለስ የሚለው ቃል ብዙ ጊዜ በምሳሌያዊ መልኩ ጥቅም ላይ ከዋለ፣ “መኖር” ማለት ነው።
መመሪያ በተወሰነ ማኅበረሰብ ውስጥ ያሉ ሰዎች የሚያከብሩት ሕዝባዊ ደንብ ወይም ትእዛዝና መመሪያ የሚሰጥ ሕግ ነው።
“መመደብ” ወይም፥ “መደበ” የሚለው ቃል የተወሰነ ተግባርን እንዲፈጽም አንድን ሰው መሾምን ያመለክታል
“መምራት” እና፣ “መመሪያ” የተሰኙ ቃሎች የሚያመለክቱት አንድን ነገር እንዴት ማድረግ እንደሚቻል ወይም መታዘዝ የሚገባ ሕግን አስመልክቶ ግልጽ የሆነ አቅጣጫ መመልከት ማለት ነው።
እርስ በርስ የሚመሳሰሉ ሰዎች ወይም ነገሮች እርስ በርስ የሚጋሩዋቸው ነገሮች ይኖሯቸዋል።
እርስ በርስ የሚመሳሰሉ ሰዎች ወይም ነገሮች እርስ በርስ የሚጋሩዋቸው ነገሮች ይኖሯቸዋል።
“መምከር” ጠንከር አድርጎ ማስጠንቀቅ ወይም ምክር መስጠት ማለት ነው።
“መሠረተ” የሚለው ግሥ አንድ ነገር ላይ ሠራ ወይም ገነባ ማለት ነው። መሠረት አንድ ሕንፃ የሚያርፍበት ከታች ያለው አካል ነው።
“ቁርባን” (ስጦታ) የሚለው ለእግዚአብሔር ወይም ለጣዖት የተሰጠ ማንኛውንም ነገር የሚያመለክት አጠቃላይ ቃል ነው። መሥዋዕት በብዙ መልኩ ይመሳሰላል፤ ሆኖም በተለምዶ ከተገደሉ በኋላ ለእግዚአብሔር ወይም ለጣዖት የሚሰጡ ነገሮችን ያመለክታል
“መረዳት” መረጃ መስማት ወይም መቀበልና ምን ማለት እንደሆነ መገንዘብ ማለት ነው።
ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “መሰናከል” እየተራመዱ ወይም እየሮጡ እያል የመውደቅ ያህል መንገዳገድ ማለት ነው። ብዙውን ጊዜ በአንድ ነገር መደናቀፍን ያመለክታል
“መሰናከያ” ወይም፣ “መሰናከያ ድንጋይ” አንድ ሰው ተደናቅፎ እንዲወድቅ የሚያደርግ ነገርን ያመለክታል
አንድ ሰው ከንፈሮቹን አጥብቆ ሌላው ሰው ጉንጮች ወይም ከንፈሮች ላይ በማድረግ ፍቅሩን የሚገልጥበት ሁኔታ ነው፥
“መሳት” እና “ሳተ” በእግዚአብሔር ፈቃድ ላይ መመፅ ማለት ነው። “ወደ ስህተት መመራት” ሌሎች ሰዎች ወይም ሁኔታዎች ለእግዚአብሔር ወዳለመታዘዝ እንዲመራቸው መፍቀድ ማለት ነው
አንድን ነገር መስቀል ያንን ነገር ከመሬት በላይ ማንጠልጠል ማለት ነው።
ስለ እርሱ ለማስተማርና ለእርሱ እንዲታዘዙ ለማሳሰብ ለተወሰኑ ሰዎች መናገር ማለት ነው።
መስከር የአልኮል መጠጥ አብዝቶ በመጠጣት አእምሮን መሳት ወይም ከተለመደው የተለየ ፀባይ ማሳየት ማለት ነው።
በዚህ አግባብ መሠረት፥ “መስጠት” ሲባል አንድን ነገር ለማድረግ መወሰን ወይም ቃል መግባት ማለት ነው።
ቃል በቃል ከተወሰደ፣ “መሸከም” አንድን ነገር ራስ ላይ መጫን ማለት ነው። ይህ ቃል በርካታ ምሳሌያዊ ጠቀሜታዎችም አሉት።
“መሸፈኛ” ብዙውን ጊዜ የሚያመለክተው ራስን ለመሸፈን የሚያገለግለውን በጣም ስስ ልብስ ሲሆን፣ ራስና ፊት እንዳይታይ ይከልላል።
መሾም ሲባል ወግ ባለው ሁኔታ ለተለየ ተግባር ወይም ድርሻ አንድን ሰው መለየት ማለት ነው። በዐዋጅ ደረጃ ሕግን ወይም ደንብን ማሳወቅ ማለትም ይሆናል።
“መቀበል”የሚለው ቃል ለአንድ ሰው ወይም ሁኔታ ተገቢ ዕውቅና ወይም ይሁንታ ሲሰጠው ማለት ነው።
“መቀበል” የተሰጠ ወይም የቀረበ ነገርን ተቀብሎ የራስ ማድረግ ማለት ነው።
መቀደስ ለአንድ ራሱን ለቻለ ዓላማ ወይም ተግባር አንድን ነገር መለየት ወይም መስጠት ማለት ነው።
‘’መቀጣት’’ ወይም ‘’ቁጣ’’አንድ ነገር ወይም ሰወ ላይ ደስ አለመሰኘት፤መበሳጫትና መናደድ ማለት ነው፤
“መቁረጥ” የሚለው ቃል ማግለልን፣ ማስወገድን ወይም ከዋው ወገን መነጠልን ለማመልከት ጥቅም ላይ ይውል የነበረ ፈሊጣዊ ቃል ነው። ከኀጢአት የተነሣ በመልኮታዊ ፍርድ መገደልን ሊያመለክትም ይችላል።
“መቃብር” እና፣ “የቀብር ቦታ” ሰዎች የሞተውን ሰው አካል የሚያኖሩበት ስፍራ ነው።
“መቃተት” የሚለው ቃል ከአካላዊ ወይም ስሜታዊ ሕመም የተነሣ ከጥልቅ የሚወጣ አጭር ድምፅ ነው። ብዙውን ጊዜ መቃተት የሚገለጠው ያለ ምንም ቃል ነው።
አንድን በር ደግፎ የሚይዝ በሩ ግናራ ቀኝ ላይ ያለ ቀጥ ያለ ጣውላ ነው።
“መቅለጥ” የሚለው ቃል ሙቀት ሲነካው የአንድ ነገር ፈሳሽ መሆንን ያመለክታል። ምሳሌያዊ በሆነ መልካም ጥቅም ላይ ይውላል።
መቅሠፍት የሚባለው ብዙ ሕዝብ ላይ ጉዳት ወይም ሞት የሚያስከትል በሽታ ወይም ሌላ ሁኔታ ነው።
“መቅበር” የሞተ ሰውን አካል ጉድጓድ ውስጥ ወይም ሌላ መቀበፊያ ቦታ ውስጥ ማኖርን ያመለክታል። “ቀብር” የሚለው ቃል አንድ ነገር የመቅበር ሥራ ሲሆን፣ አንድን ነገር ለመቅበር የሚያገለግል ቦታንም ያመለክታል።
“ቅጣት” ከፈጸመው ጥፋት የተነሣ አንድ ሰው ላይ አሉታዊ ውጤቶች ማድረስ ማለት ነው።
“መበልጸግ” አንድ ሰው ወይም ሕዝብ በሕይወታቸው ሲከናወኑ ወይም የተሳካላቸው ሲሆኑ ማለት ነው። ይህ መከናወን ቁሳዊ ወይም መንፈሳዊ ሊሆን ይችላል። “ብልጽግና” ሀብታምና ደኅና የመሆን ሁኔታ ነው።
“መበቀል” ወይም፥ “በቀል” እርሱ ላደርሰው ጉዳት ለመክፈል ሲባል አንድን ሰው መቅጣት ማለት ነው። የመበቀያ ወይም በቀል የተፈጸመበት ተግባር “ብቀላ” ይባላል
መበታተን የሰዎችን ወይም የነገሮችን በተለያዩ አቅጣጫ መበታተን ያመለክታል።
ይህ ቃል የሚያመለክተው በአደገኛ ሁኔታ መብላትን ወይም ጨርሶ ማቃጠልን ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ሰዎች ይጠቀሙበት የነበረው መብራት በሚነድበት ጊዜ ብርሃን የሚሰጥ ብዙውን ጊዜ እንደ ኀይል ሰጪ የሚያገለግል ዘይት የያዘ ዕቃ ነበር።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “መብራት መያዣ” ክፍሉ ውስጥ ሁሉ እንዲያበራ መብራቱ የሚቀመጥበት ከእንጨት ወይም ከብረት የተሠራ ዕቃ ነው።
“መብዛት” የሚለው በከፍተኛ ደረጃ በቁጥርና በመጠን ማደግን ያመለክታል።
“መተርጎም” እና፣ “ትርጉም” የተሰኙት ግልጽ ያልሆነ ነገርን መርዳትና ያንን ግልጽ ማድረግን ያመለክታል።
እነዚህ ቃሎች ከሞት ጋር የሚያያዝ ምሳሌያዊ ትርጉም አላቸው
መታሰቢያ የሚለው ቃል አንድ ሰው ወይም አንድ ሁኔታ እንዲታሰብ የሚያደርግ ተግባር ወይም ነገር ማለት ነው።
“የታወቀ” የሚለው ቃል ሰፊ ተቀባይነት ማግኘትፍንና ስመ ጥሩ የሆነ ሰውን ያመለክታል።
“መታዘዝ” ሥልጣን ያለው ሰው የሚፈልገውን ወይም እንዲደረግ የሚያዝዘውን መፈጸም ማለት ነው። “ታዛዥ” የተነገረውን ወይም የታዘዘውን የሚፈጽም ሰው ነው።
አንድን ሰው መታደግ እርሱን ማዳን ማለት ነው። ታዳጊ ከባርነት፣ ከጭቆና ወይም ከሌላ አደጋ ሰዎችን የሚታደግ ወይም ነጻ የሚያወጣ ነው።
መታገሥ ረጅም ጊዜ መቆየት ወይም አስቸጋሪ ነገርን መቋቋም ማለት ነው።
“መታጠቂያ” የሚለው ቃል አንዳች ነገር ዙሪያ የሚታሰር ነገርን ነው። ብዙ ጊዜ የሚያመለክተው ቀሚስ ወይም እጀ ጠባብ ወደ መሬት እንዳይወርድ ወገብ ላይ ለማሰር የሚያገለግል ቀበቶ ወይም ሻሽን ነው።
በአጠቃላይ፣ “መነሣት” – “ብድግ ማለት” ወይም፣ “ወደ ላይ መውጣት” ማለት ነው።
“መነፋት” የሚለው ፈሊጣዊ ቃል የሚያመለክተው ትዕቢተኛ ወይም ዕብሪተኛ መሆንን ነው።
“መናቅ” አንድ ሰው ወይም አንድን ነገር ለመቀበል አለመፈለግ ማለት ነው። እግዚአብሔርን መናቅ ለእርሱ መታዘዝ አለመፈለግ ነው።
“መንቀጥቀጥ” ከፍርሃት ወይም ከከባድ ጭንቀት የተነሣ መናወጥ ወይም፣ መንዘፍዘፍ ማለት ነው።
“መንጋ” በጎችንና ፍየሎችን ወይም በሬዎችንና ላሞችን ወይም አሳማዎችን ያመለክታል
መንግሥት በንጉሥ የሚገዛ የሰዎች ቡድን ነው። ንጉሥ ወይም ሌሎች ገዦች የሚቆጣጠሩትና በሥልጣን የሚያስተዳድሩትንም አካባቢ ወይም ፖለታካዊ አገርንም ያመለክታል።
ብዙውን ጊዜ፣ “መንጠቅ” የሚለው ቃል ተአምራዊ በሆነ መንገድ እግዚአብሔር በድንገት አንድን ሰው ወደ ሰማይ ሲወስድ ነው።
“መንጠቅ” የሚያመለክተው አንድን ነገር፣ ብዙውን ጊዜ ደግሞ ለምግብ የሚሆን እንስሳን ማደንን ነው።
“መከራ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው መከራና ጭንቀት ያለበት አዳጋች ጊዜን ነው።
“መከራ ማድረስ” አንድን ሰው ማሰቃየት ወይም መጉዳት ማለት ነው። “መከራ” ከዚህ የሚመጣ ሕመም፣ ስሜታዊ ሐዘን ወይም ሌላ ዐይነት ጉዳት ነው።
“መከራ” እና፣ “መከራ መቀበል” የተሰኙት ቃሎች በሽታን፣ ስቃይን ወይም ሌሎች አዳጋች ነገሮችን የመሳሰሉ አስከፊ ነገሮች ማለት ነው
“መከር” የሚለው ቃል እህል፣ ፍራፍሬ ወይም አትክልት መሰብሰብን ያመለክታል።
“መካን” መሆን ልጅ አለመውለድ ወይም ፍሬያማ አለመሆን ማለት ነው
መካከለኛ የሚባለው ሁለት ወገኖች አለመግባባትን አስወግደው ዕርቅ እንዲያደርጉ የሚረዳ ሰው ነው።
“መክሰስ”እና “ክስ” የተሰኙት ቃሎች በደል በማስረጉ አንድን ሰው መወቀስን ያመለክታል።ሌሎችን የሚከስ ሰው ከሳሽ ይባላል።
“መክበብ” የሚለው ቃል አጥቂ ሰራዊት ከተማን ሲከብና ምግብም ሆነ መጠጥ ወደዚያ እንዳይገባ ማድረግን ያመለክታል። አንድን ከተማን መክበብ እንቅስቃሴዋን መቆጣጠር ማለት ነው
“መወሰን” የሚለው ቃል ወደ ፊት ሰዎች ላይ የሚደርሰውን ያመለክታል። አንድ ሰው አንዳች ነገር እንዲያደርግ፣ “ተወስኖ” ከሆነ ያ ሰው ወደ ፊት የሚያደርገውን እግዚአብሔር ወስኖታል ማለት ነው።
“ማረድ” አንድ ሰው እንዲያፍር ወይም እንዲሸማቀቅ ማድረግ ማለት ነው። ብዙውን ጊዜ ይህ የሚደረገው ሰዎች ፊት ነው።
“ማረድ” አንድ ሰው እንዲያፍር ወይም እንዲሸማቀቅ ማድረግ ማለት ነው። ብዙውን ጊዜ ይህ የሚደረገው ሰዎች ፊት ነው።
“መዋረድ” ክብርንና ተቀባይነት ማጣትን ያመለክታል።
“መውቂያ” እና፣ “መውቃት” የተሰኙት ቃሎች የስንዴን ዘር ከተቀረው የስንዴው ክፍል የመለየት ሥራን ያመለክታሉ።
“መውጋት” ስለት ባለው ሹል ነገር መውጋት ማለት ሲሆን፣ ምሳሌያዊ በሆነ መልኩ ሰውን በጣም ማሳዘንን ለማመልከትም ጥቅም ላይ ይውላል።
“መያዝ” አንድን ሰው ወይም አንድን ነገር በኅይል መያዝ ማለት ነው። ማሸነፍ ወይም ከቁጥጥር ሥር ማድረግ ማለትም ይሆናል
“መያዝ” ሰው ላይ ወይም አንዳች ነገር ላይ ተቆጣጣሪ መሆን ማለት ነው። አብዛኛውን ጊዜ አንድ ነገር አሳድዶ መያዝንም ይጨምራል።
“መደምሰስ” እና፣ “ደመሰሰ” የሚለው ቃል ሰዎችን ወይም ነገሮችን ጨርሶ ማስወገድ ወይም ማጥፋትን የሚያመለክት ፈሊጣዊ ቃል ነው።
መደረቢያ ከትከሻ እስከ ወገብ ወይም ጉልበት የሚደርስ ልብስ ነው።
እነዚህ ቃሎች “አንድ የተለየ ነገር በመደረጉ መደነቅን” ነው የሚያመለክቱት።
“አክብሮት” የሚለው የመደነቅ ስሜትንና ታላቅነትን፥ ኅያልነትንና ባለ ግርማነትን በማየት የሚመጣ ጥልቅ አክብሮትን ያመለክታል
“መደፋት” የሚለው ቃል ፊትን ወደ መሬት በማድረግ መዘርጋት ማለት ነው። በድንገት በጣም ዝቅ ብሎ ማጎንበስ ማለት ነው።
መገሠጽ በቃል ጠበቅ ያለ እርማት መስጠት ሲሆን፣ ብዙውን ጊዜ እንዲህ የሚደረገው ያንን ሰው ከኀጢአት ለመመለስ ነው።
ብዙውን ጊዜ፣ “መገዛት” የሚለው ቃል ፈቅዶና ወዶ ራስን በሌላው ሰው ሥልጣን ወይም መንግሥት ሥር ማድረግ ማለት ነው
መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን “መጋረጃ” የሚያመለክተው መገናኛው ድንኳንንና ቤተ መቅደሱን ለመሥራት ጥቅም ላይ ይውል የነበረውን ወፍራምና በጣም ከባድ ጨርቅ ነበር።
መግዛት በአንድ አገር ወይም በአንድ መንግሥትና ሕዝቡ ላይ ንጉሥ መሆን ማለት ነው። አንድ ንጉሥ የሚገዛው እርሱ በሕይወት እስካለ ድረስ ነበር።
ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “መግፋት” ጉልበት በመጠቀም አንድን ነገር ማስወገድ ማለት ነው። የተለያዩ ምሳሌያዊ ጠቀሜታዎችም አሉት።
“መጠበቂያ ግንብ” ጠባቂዎች እዚያ ላይ ሆነው ማንኛውንም አደጋ የሚመለከቱበት ቦታ እንዲሆን የተሠራ ረጅም ግንብ ነው። እነዚህ ግንቦች አብዛኛውን ጊዜ የሚሠሩት ከድንጋይ ነው።
“መጠየቅ” መረጃ የሚጠይቅ ማለት ነው።
“መጠጊያ” የሚለው ቃል ዋስትናና ጥበቃ ያለበትን ቦታን ወይም ሁኔታን ያመለክታል። “መጠቢያ” ከዝናብ ወይም ከአደጋ የሚከልል ነገር ነው።
“መጠጊያ” የሚለው ቃል ዋስትናና ጥበቃ ያለበትን ቦታን ወይም ሁኔታን ያመለክታል። “መጠለያ” ከዝናብ ወይም ከአደጋ የሚከልል ነገር ነው።
“መጥረግ” እና፣ “ጠረገ” የሚሉት ቃሉች አብዛኛውን ጊዜ የሚያመለክቱት መጥረጊያ በመጠቀም ቆሻሻና የማይፈለግ ነገር ማስወገድ በፍጥነት መንቀሳቀስን ነው። እነዚህ ቃሎች ማሳሌያዊ ትርጉምም አላቸው
ቃል በቃል ሲወሰድ እስኪያልቅ ድረስ አንድን ነገር መጠቀም ማለት ሲሆን በርካታ ምሳሌያዊ ትርጕሞችም ይኖሩታል።
“መጨቆን” እና፣ “ጭቆና” በከፍተኛ ደረጃ ሰዎችን መበደልን ያመለክታል። “ጨቋኝ” ሰዎችን የሚጨቁን ሰው ነው።
“መጮኽ” እንባ አውጥቶ ማልቀስ ወይም ጭንቅ ውስጥ ያለ ሰው የሚያሰማው ጥሪ ሊሆን ይችላል።
መጽናት፣ ምንም እንኳ ረጅም ጊዜ ቢወስድና በጣም አስቸጋሪም ቢሆን በእምነት ወይም የተሰጠውን ሥራ በመፈጸም መቀጠል ማለት ነው።
“መጽደቅ” እና፣ “ጽድቅ” የተሰኙት ቃሎች በደለኛውን ሰው ምንም በደል እንዳልፈጸመ አድርጎ መቀበል ማለት ነው። ሰዎችን ማጽደቅ የሚችል እግዚአብሔር ብቻ ነው።
ብዙዎን ጊዜ “መፅነስ” እና፣ ፅንስ” የተሰኙ ቃሎች የሚያመለክቱት ልጅ ማርገዝን ነው። ያረገዙ እንስሳትን ለማመልከትም ጥቅም ላይ ይውላል።
“መፈለግ” አንድን ሰው ወይም አንድን ነገር መሻት ማለት ነው። ኅላፊው ግሥ፣ “ፈለገ” የሚለው ነው። አንድን ነገር ለማድረግ “አጥብቆ መሞከር” ወይም፣ “ከባድ ጥረት ማድረግ” ማለትም ይሆናል
መፈወስ የሰው ቁስል፣ ሕመም ወይም ዕዐይነ ስውርነትና የመሳሰሉ ጉድለቶች ከእንግዲህ እንዳይኖሩ ማደረግ ነው። ወይም የታመመውን ወይም ዐቅም ያጣውን ሰው እንደ ገና ጤነኛ ማድረግ ነው።
መፋታት ጋብቻ የሚቋረጥበት ሕጋዊ አሠራር ነው። ፍቺ ያደረጉ ባልና ሚስት ከእንግዲህ ትዳር ውስጥ አይደሉም ማለት ነው።
አንድ ነገር፣ “ማፍረስ” ያንን ነገር ማበላሸት፣ ማጥፋት፣ መደምሰስ፣ ወይም ከጥቅም ውጪ ማድረግ ማለት ነው። “ፍርስራሽ” እንዲፈርስ ከተደረገው ነገር የቀረ ክምር ነው።
“መፍጠር” አንድን ነገር ማድረግ ወይም ሕልውና እንዲኖረው ማድረግ ማለት ነው። የተፈጠረ ነገር “ፍጥረት” ይባላል። በመላው አጽናፍ ያለውን ወደ ሕልውና ያመጣ እርሱ በምሆኑ እግዚአብሔር፣ “ፈጣሪ” ይባላል።
ሙሽሪት የወደፊት ባልዋ ከሚሆነው ሙሽራ ጋር ለመጋባት የጋብቻ ሥርዓት ላይ ያለች ሴት ናት።
ጋብቻ ሥርዓት ላይ ያለ ሙሽራ ሙሽራዪቱን የሚያገባው ሰው ነው።
“ማልቀስ” እና፣ “ለቅሶ” የተሰኙት ቃሎች ጥልቅ የሐዘን መገለጫዎች ሲሆኑ፣ ብዙውን ጊዜ የሚያያዙት ሰው ሲሞት ከሚደረግ ሐዘን ጋር ነው። ብዙ ባሕሎች ሐዘንና ትካዜያቸውን የሚገልጡበት ውጫዊ እንቅስቃሴን ይጨምራል።
“ማሕፀን” እናቱ ውስጥ ያለ ሕፃን የሚኖርበት ነው።
ማመፅ ሥልጣን ላይ ላለ ሰው አለመገዛት ማለት ነው። ለአለቃ አለመታዘዝ ማለትም ነው።
“ማረሻ” አንድን ቦታ ለዘር ለማዘጋጀት መሬቱን ሥርዓት ባለው መልኩ ለመቆፈር የሚያገለግል የእርሻ መሣሪያ ነው።
“ማረድ” ሰውን ወይም እንስሳን መግደል ማለት ነው። ብዙ ጊዜ ግን በኅይል ወይም በአሰቃቂ ሁኔታ መግደልን ነው የሚያመለክተው
“ማረድ” ሰውን ወይም እንስሳን መግደል ማለት ነው። ብዙ ጊዜ ግን በኅይል ወይም በአሰቃቂ ሁኔታ መግደልን ነው የሚያመለክተው
ማር ንቦች ከአበባ የሚሠሩት ጣፋጭና ሙጫነት ያለው የሚበላ ነገር ነው። የማር እንጀራ ንቦቹ ማሩን የሚያኖሩበት እንደ ሰም ያለው ቅርጽ ነው።
“ማርከስ” ቅዱስ የሆነ ነገርን ማቆሸሽ፣ መበከል ወይም አለማክበር ማለት ነው።
“ማርከስ” እና፣ “መርከስ” የተሰኙት ቃሎች መበከልን ወይም በከፍተኛ ደረጃ መቆሸሽን ያመለክታሉ። አንድ ነገር ከአካላዊ፣ ከግብረ ገባዊ ወይም ከሃይማኖታዊ ሥርዓት ጋር በተያያዘ ርኵስ ተብሎ ሊጠራ ይችላል።
ለአምልኮ ጥቅም ላይ ማዋል በማይቻልበት ሁኔታ የተቀደሰ ቦታን ወይም ነገርን መጉዳት ወይም መበከል ማለት ነው።
“ማሰላሰል” የሚለው ቃል ጊዜን ወስዶ ስለ አንድ ነገር በጥንፍቃቄና በጥልቀት ማሰብ ነው።
“ማሳሳት” እውነት ያልሆነ ነገር እንዲታመን ማድረግ ነው። ሌሎችን የማሳሳት ተግባር “ማሳት” ይባላል።
አንድን ሰው ማሳደድ ደጋግሞ ማጥቃት ወይም እርሱ ላይ የጭካኔ ተግባር መፈጸም ነው።
“ማስተማር” ከዚያ በፊት የማያውቁትን መረጃ ለሰዎች መናገርን ያመለክታል። ብዙውን ጊዜ መረጃው የሚሰጠው ወግ ባለው ወይም ስልታዊ በሆነ መንገድ ነው
ማስጠቀቂያ የሚጎዳቸውን ነገር አስመልክቶ ሰዎችን ማሳሰብ ማስጠንቀቅ ማለት ነው።መሸበር አደገኛ ወይም ስጋት ያለውን ነገር በተመለከተ በጣም መጨነቅና መፍራት ማለት ነው።
ማቅ ከፍየል ወይም ከግመል ጠጉር የሚሠራ ልብስ ነው። ይህ ዐይነቱ ልብስ ሻካራና የሚኮሰኩስ ነበር።
መበረታታት የሚለው የሚያመለክተው በቃልም ሆነ በተግባር ሌሎች እንዲጽናኑ፣ ተስፋ እንዲኖራቸው፣ ድፍረትና ጽናት እንዲኖራቸው ማድረግን ነው።
“ማበራየት” እና፣ “ማበጠር” ለምግብ የሚሆነውን እህል ከማይፈልጉ ነገሮች መለየት ማለት ነው። ስሞችን መለየትን ወይም መክፈልን አስመልክቶ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሁለቱም ቃሎች በምሳሌያዊ መልኩ ጥቅም ላይ ውለዋል።
አንድን ነገር ማባከን በቸልታ መወርወር፣ ወይም ያለ አግባብ መጠቀም ማለት ነው። “የባከነ” የጠፋ ወይም ከጥቅም ውጪ የሆነ ነገርን ያመለክታል።
“ማነሣሣት” ወይም፣ “መተንኮስ” አንድ ሰው አሉታዊ ምላሽ እንዲሰጥ ወይም አሉታዊ ስሜት እንዲያድርበት ማድረግ ማለት ነው።
አንድ ሰው ወይም ነገር ምን ያህል ታላቅና አስፈላጊ መሆኑን ማሳየት ወይም መናገር ማለት ነው። ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “ክብር መስጠት” ማለት ነው።
“ማወቅ” አንድን ነገር መረዳት ወይም አንድን ሐቅ መገንዘብ ማለት ነው። “ማሳወቅ” አንድን መረጃን ለሌሎች መናገር ማለት ነው።
“ማወጅ” እና “ዐዋጅ” የተሰኙት ቃሎች የሚያመለክቱት ሰው ሁሉ እንዲያውቀው ተፈልጎ በግልጽ በአደባባይ ለሕዝብ የሚነገር ሲሆን፣ እንዲህ የሚደረገው ለጉዳዩ አጽንዖት ለመስጠት ታስቦ ነው።
አንድን ነገር በሕዝብ ፊት እና በድፍረት መናገር ወይም ማሳወቅ ማወጅ ይባላል።
“ማወደም” ወይም፣ “ውድመት” የተባለው ቃል ንብረትን፣ ምድርን ወይም ሌላ ጠቃሚ ነገርን ጨርሶ ማጥፋትን ያመለክታል። ብዙውን ጊዜ በዚያ ምድር የሚኖሩ ሰዎችን መቆጣጠርን ወይም ጨርሶ ማጥፋትንም ይጨምራል።
አንድ ነገር ወይም አንድን ሰው፣ “ማውጣት” ወይም፣ “ማባረር” ያ ነገር ወይም ሰው ከዚያ እንዲሄድ ማስገደድ ማለት ነው።
“ማዳፈን” የሚለው ቃል አንድ ነገር ማጥፋት ወይም መርካት የሚፈልግን ነገር ማስቆም ማለት ነው።
“ማድላት እና፣ “አድልዎ” የተሰኙ ቃሎች፣ አንዳንድ ሰዎችን ከሌሎች የበለጠ ማቅረብ ወይም ከሌሎች የተለየ ነገር ማድረግን ያመለክታል።
አንድን ሰው ማገለገል ለእርሱ የሚጠቅመውን ማድረግ ማለት ነው። አንድ ሰው ሌላውን የሚያገለግለው፣ ተገድዶ ወይም ማገልገል ስለፈለገ ብቻ ሊሆን ይችላል
ማጎንበስ ለአንድ ሰው ክብርን ለማሳየት በትሕትና ከወገብ እጥፍ ማለት ነው። “ጎንበስ ማለት” በጣም መታጠፍ ወይም በጣም ዝቅ ብሎ መንበርከክ ማለት ሲሆን፣ ብዙውን ጊዜ ግንባርንና እጆችን መሬት ላይ ማድረግንም ይጨምራል።
ማጨድ እህልን የመሳሰሉ ነገሮች ማምረት ማለት ነው። እህል የሚያመርት ሰው አጫጅ ይባላል።
“ማጽናት” የሚለው ቃል አንድ ነገር እውነት ወይም እርግጥ ወይም አስተማማኝ መሆኑን መናገር ወይም መመልከት ማለት ነው።
“ማጽናናት” እና “አጽናኝ” የተሰኙት ቃሎች አካላዊም ይሁን ጉዳት ያደረሰባቸው ሰዎች መርዳትን፣ አይዞአችሁ ባይነትን ነው የሚያመለክተው።
“ማፌዝ” “መቀለድና” እና፣ “መዘበት” የተባሉት ቃሎች ሁሉ የሚያመለክቱት በሚጎዳ መልኩ ሌሎችን መሳቂያ መሳለቂያ ማድረግን ነው።
“ምሕረት” ይቅር ማለትና ስል ተፈጸመው ኀጢአት አለመቀጣት ማለት ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን፣ “ምሥጢር” የማይታወቅ ወይም ለመረዳት የሚያዳግት አሁን ግን እግዚአብሔር የገለጠውን ነገር ያመለክታል።
“ምርመራ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው፣ “ማጣራትን” ወይም፣ መፈተንን ነው። አንድ ሰው በደለኛ ወይም ንጹሕ መሆኑን ለማረጋገጥ የሚደረግ የማጣራት ወይም፣ የምርመራ ተግባር ነው። ምርመራ ወይም ፈተና ለመቋቋም የሚያዳግት ሁኔታ ሲሆን፣ ለዚያ በሚሰጠው ምላሽ አንድ ሰው ለተፈለገው ነገር ተገቢ ሊሆን ወይም ላይሆንን ይችላል።
ምርኩዝ ሰዎች ሲራመዱ የሚጠቀሙበት ከእንጨት ወይም ከብረት የተሠራ ከዘራ ወይም በትር ነው
“ምርኮ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ከአገራቸው ርቀው ሌላ ቦታ እንዲኖሩ የተገደዱ ሰዎችን ያመለክታል።
“ምርኮና” እና፣ “ምርኮ” የተሰኙ ቃሎች መኖር በማይፈልጉበት የባዕድ አገር እንዲኖሩ ሰዎችን መያዝ ወይም ማስገደድን ያመለክታሉ።
ምሳሌ ጥበብ ወይም እውነት የያዘ አጭር ዐረፍተ ነገር ነው።
እነዚህ ቃላት በጠቅላላ ሀሰተኛን አምላክ ለማምለክ የተቀረጹን ጣኦታትን ለማመልከት የምንጠቀምባቸው ናቸው።
“ምስክር” የሆነውን ነገር በግል የሚያውቅ ማለት ነው። ብዙውን ጊዜ ምስክር የሚባለው እውነት መሆኑን የሚያውቀውን የሚናገር ሰው ነው። “የዓይን ምስክር” እዚያ የነበረና የሆነውን ሁሉ በዓይኑ የተመለክተ ሰው ነው።
አንድ ሰው ማመስገን ለዚያ ሰው ያለንን አድናቆትና ክብር መግለጥ ማለት ነው።
“ምሽግ” ወይም፣ “መከላከያ” የጠላት ወታደሮችን ጥቃት መከለከል እንዲቻል በሚገባ የታጠረ ወይም ከለላ ያለው ቦት ማለት ነው። “የተመሸገ” ከተባለ አንድን ከተማ ወይም ምሽግ ለመከላከል በጠንካራ ግንቦች ዐለቶችና ሌሎች ጠንካራ ነገሮች ማጠርን ያመለክታል
ምንጭ በተፈጥሮው ከመሬት የሚፈልቅ ወይም የሌላ ዓይነት ወራጅ ውሃ መነሻ ቦታ ነው።
ምክር ማለት አንድ ሰው ማስተዋል ያለበት ውሳኔ እንዲያደርግ ተገቢውን ሐሳብ መስጠት ማለት ነው። መልካም “መካሪ” ወይም፣ “አማካሪ” ሰዎች ትክክልኛ ምርጫ ማድረግ እንዲችሉ አስፈላጊ ሐሳብ ይሰጣል።
“ምድር” ሕይወት ያላቸው ሌሎች ነገሮችን ጨምሮ የሰው ልጆች የሚኖሩበትን ዓለም ያመለክታል።
ምድጃ መንደድ ያለበት ነገር የሚቀጣጠልበትና የሚነድበት ትልቅ ማንደጃ ነው።
“ምጽዋት” የሚለው ቃል ድኾችን ለመርዳት የሚሰጥ ገንዘብን፣ምግብን ወይም ሌሎች ነገሮችን ያመለክታል።
እነዚህ ቃሎች አካላዊንም ሆነ መንፈሳዊ ሞትን ለማመልከት ጥቅም ላይ ይውላሉ። አካላዊ በሆነ መልኩ የሰውየው አካል መሥራትን ማቆሙን ያመለክታል። በመንፈሳዊ አንጋገር በኀጢአታቸው ምክንያት ሰዎች ከቅዱሱ እግዚአብሔር መለየታቸውን ያመለክታል።
ሟርት እና ሟርተኛ የሚለው ቃል ልዕለ ተፈጥሮአዊ ከሆነው የመናፍስት ዓለም መረጃ ለማግኘት የሚደረግ መከራን ያመለክታል። ይህን የሚለማመድ ሟርተኛ ይባላል።
“ሟርት” ወይም “ጥንቆላ” አስማት በመጠቀም በክፉ መናፍስት ርዳታ አስደናቂ ነገሮችን ማድረግን ያመለክታል። በእነዚህ አስማታዊ ኅይሎች አስደናቂ ነገሮች የሚያደርገው ሰው ሟርተኛ ይባላል
ማንኛውም ጉልበትን የሚጠቅይ ከባድ ልፋት ሥራ ይባላል።
ሥርዓት ሰዎች የሚኖሩበት መመሪያ የሚሆን በውል ጽሑፍ ላይ የሰፈረ ሕግ ነው
ሩጫ፣ መሮጥ ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “ሩጫ” ከመራመድ ባለፈ በፍጥነት መንቀሳቀስ ማለት ነው
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ራስ” በርካታ ምሳሌያዊ ትርጕሞች አሉት።
ራስን መግዛት ኅጢአትን ላለማድረግ የራስን ፀባይና ሁለንተና የመቆጣጠር ችሎታ ማለት ነው
“ራእይ” የሚለው ቃል አንድ ሰው የሚያየውን ያመለክታል። በተለይ ደግሞ የሚያመለክተው መልእክት ለመስጠት ባልተለመደ ወይም ልዕለ ተፈጥሮአዊ መንገድ እግዚአብሔር ለሰዎች የሚያሳየውን ያመለክታል።
ርግብና ዋኖስ በጣም የሚመሳሰሉ የተለያየ መልክ ያላቸው ትናንሽ ወፎች ናቸው። ርግብ በምጠኑ ፈካ ያለች ስትሆን ወደ ነጭነት ትጠጋለች።
ሮማን በሚበላ ቀይ ነገር የተሸፈኑ ብዙ ፍሬዎች ያሉት ጥብቅና ጠንካራን ሽፋን ያለው የፍራፍሬ ዐይነት ነው።
ሰላም ምንም ዓይነት ግጭት ወይም ስጋት አለመኖር ማለት ነው።
በጥንት ዘመን ሰረገሎች በፈረሶች የሚጎተቱ ቀለል ያለ ክብደት ያላቸው ባለ ሁለት ተሽከርካሪ (ጎማ) መጓጓዣ ነበሩ።
ሰኮና ግመልን፣ ላምና በሬን፣ ፈረሶችን፣ አህዮችን፣ በጎችና ፍየሎችን የመሳሰሉ አንዳንድ እንስሳት ታችኛውን የእግራቸውን ክፍል የሚሸፍን ጠንካራ ነገር ነው።
አንድ ነገር የተፈጸመው ምቼና እንዴት እንደ ነበር ከማመልከት በተጨማሪ፣ “ሰዓት” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለቻቸው በርካታ ምሳሌያዊ መንገዶች አሉ።
ሰይፍ ለመቁረጥ ወይም ለመውጋት የሚያገለግል ጠፍጣፋ ስለት ያለ የጦር መሣሪያ ነው መያዣና ረጅም፣ ሾጠጥ ያለና ጫፉ ላይ ስለት አለው
ሳንደል ከእግር ታችኛው ክፍልና ከቁርጭምጭሚት ጋር በክር የሚታሰር ሰለል ያለ ጫማ ነው። ወንዶችም ሆኑ ሴቶች ይጠቀሙበት ነበር
ሴላ ብዙውን ጊዜ መዝሙር መጽሐፍ ውስጥ የሚገኝ የዕብራይስጥ ቃል ነው በርካታ ትርጉሞች ይኖሩት ይሆናል
‘’ስቃይ” የሚለው ቃል ከባድ ህመምን ወይም ጭንቀትን ያመለክታል።
“ስቃይ” የሚያመለክተው ከፍተኛ መከራን ነው። አንድን ሰው ማሰቃየት ብዙውን ጊዜ በጭካኔ ከባድ መከራ እንዲደርስበት ማድረግ ነው።
“ስብሰባ(ጉባኤ)” የሚለው ቃል ችግሮች ላይ ለመወያየት፥ ምክር ለመስጠትና ውሳኔ ለማሳለፍ በአንድነት የተሰበሰቡ ሰዎችን ያመለክታል
ስንዴ ሰዎች ለምግብ የሚያመርቱት እህል ነው።
ሸንጎ በጣም አስፈላጊ ጉዳዮችን በተመለከት ለመወያየት፣ ምክር ለመስጠትና ውሳኔ ለማሳለፍ የተሰበሰቡ ሰዎች ማለት ነው።
ሸክም ከባድ ጫና ነው። ቃል በቃል የጥንት እንስሳት የሚሸከሙትን ሸክም ያመልክታል። “ሸክም” የሚለው ቃል በርካታ ምሳሌያዊ ትርጕሞችም አሉት።
ሽማግሌዎች በእግዚአብሔር ሕዝብ መሐል መንፈሳዊና ተግባራዊ መሪነት ኀላፊነት ያላቸው መንፈሳዊ ማስተዋል ያላቸው ስሞች ናቸው።
“ሽብር” የሚለው ቃል በጣም የመፍራትና የመደንገጥ ስሜት ወይም አንድን ሰው ወይም ነገር በጣም መጥላት ማለት ነው።
“ሽብር” የሚለው ቃል ከፍተኛ የፍርሃት ወይም የድንጋጤ ስሜት ያመለክታል። ሽብር የሚሰማው ሰው፣ “ተሸበረ” ይባላል።
“ቀረጥ” ሰዎች እነርሱ ላይ ሥልጣን ላይ ላለው መንግሥት የሚከፍሉት ገንዘብ ወይም ዕቃ ነው
የቀረጥ ሰብሳቢ ሥራ ከሰዎች የተቀበለውን ገንዘብ ለመንግሥት ማስተላለፍ ነበር
“ቀንበር” ሁለት በሬዎች በአንድነት እንዲሠሩ ለማጣመር የሚረዳ ነገር ነው። “ቀንበር መሸከም” አንድ ዓይነት ኀላፊነት መሸከም ማለት ነው።
ቀንዶች ላምና በሬ፣ በጎችና ፍየሎች የመሳሰሉ እንስሳት ራስ ላይ የሚበቅል ቋሚና ሹል ነገር ነው። ብርታትን፣ ኀይልን፣ ሥልጣንና ንጉሥነትን ለማመልከትም “ቀንድ” በምሳሌያዊ መልኩ ጥቅም ላይ ይውላል።
“ቃል” አንድ ሰው የተናገረውን ያመለክታል።
“ቃል መግባት” አንድ ነገር ለማድረግ ወይም ለመስጠት ተስፋ መስጠት ማለት ነው።
ቃርሚያ አጫጆች የተዉትን ፍራ ፍሬ ወይም እህል ለመሰብሰብ እርሻ ወይም አትክልት ቦታ ውስጥ መሄድ ማለት ነው።
“ቅርጫት” እርስ በርስ ከተጠላለፉ ነገሮች የሚሠራ መያዣን ያመለክታል
ቅርጽ ማውጫ የሚባለው ከወርቅ፣ ከብርና ከሌሎች ፈሳሽ መሆን ከሚችሉ ነገሮች አንዳንድ ነገሮችን ለመሥራት የቅርጽ ማውጫውን ይዘው እንዲወጡ ለማድረግ ከእንጨት ቁራጭ፣ ከብረት ወይም ከሸክላ ተፈልፍሎ የሚሠራ ነገር ነው።
ቅናት ያ ሰው ካለው ሀብት የተነሣ ወይም የሚደነዙ ችሎታዎች በለቤት ከመሆኑ የተነሣ ሌላውን ሰው መመቅኘት ማለት ነው። “መመኘት” ያ ሰው ያለውን ነገር ለራስ ለማድረግ አጥብቆ እስከ መፈለግ ድረስ በቅናት መነሣሣት ማለት ነው።
“ቅን” እና፣ “ቅንነት” የእግዚአብሔርን ሕግ እየተከተሉ መኖርን ያመለክታል።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ቅድስት ከተማ” የሚያመለክተው የኢየሩሳሌም ከተማን ነው።
“ቆጠራ” የሚለው ቃል ሥርዓት ባለው መልኩ በአገሩ ወይም በመንግሥቱ ውስጥ ያሉ ሰዎች መቊጠርን ያመለክታል።
በለስ የበለስ ዛፍ ላይ የሚበቅል ትንሽና ጣፋጭ ፍሬ ነው። ሰዎች ትኩሱን፣ ቀቅለው ወይም አድርቀው በለስ መብላት ይችላሉ፣ ወይም ይከትፏቸውና እንደቂጣ አድርገው ይበሏቸዋል።
በረሐ ወይም ምድረ በዳ በጣም ጥቂት ተክሎችና ዛፎች ብቻ የሚያድጉበት ደረቅና ጠፍ ቦታ ነው።
“በረዶ” ተራሮችን በመሳሰሉ ከፍታ ቦታዎች ወይም የዓለማችን ሰሜን ወይም ደቡብ ጫፍ ላይ የሚወርድ ውሃ አዘል ጠጣር ነገር ነው
በሬ በተለይ ለእርሻ ስራ የተገራ የከብት ዓይነት ነው። ብዙ ቁጥስ ሲሆን፣ “በሬዎች” ይባላል። በሬ የሚያገለግለው ለተባዕቱ ብዙውን ጊዜ እንዲኮላሹ ይደረጋል።
“በር” ቤት ወይም ከተማ አጥር ወይም ግድግዳ ላይ ያለ ወደ ቤት የሚገባበት ላይ የተያያዘ ከለላ ነው። “የበር ሳንቃ” በርን ለመዝጋት መንቀሳቀስ የሚችል ከእንጨት ወይም ከብረት የተሠራ ጣውላ ነው።
?
“በትረ መንግሥት” አንድ ንጉሥ ወይም የአገር አስተዳዳሪ የሚይዘው ጌጠኛ በትር ወይም ዱላ ነው
በትር ቀጭን፣ ጠንካራና በተለያየ መንገድ ጥቅም ላይ የሚውል ከዘራ መሰል ነገር ነው። ምናልባትም በትንሹ አንድ ሜትር ያህል ሊረዝም ይችላል።
አጠቃላይ በሆነ መልኩ በኣል የማኅበረሰቡ ሰዎች በአንድነት የሚያከብሩት ሁኔታ ነው።
“በኩራት” የሚለው ቃል የሚያመለክተው በእያንዳንዱ መከር ወቅት ከሚሰበሰበው እህል ሆነ አትክልት የመጀመሪያውን ፍሬ ነው።
“በኩር” የሚለው ቃል መጀመሪያ የሚወለደውን የሰውም ሆነ የእንስሳትን የመጀመሪያ ልጅ ነው።
በዓል ሰዎች በአንድነት ተሰብስበው በመመገብ የሚይሳልፉት ሁኔታ ሲሆን፣ እንዲህ የሚደረገው አንድን ሁኔታ አብሮ ለማክበር ሊሆን ይችላል። “በዓል ማድረግ” በልዩ አይነት ሁኔታ የተዘጋጀ ምግብ በብዛት መመገብን ያሳያል።
በደል፣ በመደልና መጉዳት ሌላው ሰው ላይ አካላዊ፣ ስሜታዊና ሕግን ተገን በማድረግ ጉዳት ማድረስ ማለት ነው።
በገና ባለ ገመድ የሙዚቃ መሣሪያ ሲሆን፣ ቀጥ ያሉ ክሮች ወይም ገመዶች ይኖሩታል።
በግ አካሉ ላይ የሱፍ መሥሪያ ጠጉር ያለው መጠነኛ ቁመት ያለው ባለአራት እግር እንስሳ ነው። ወንዱ በግ አውራ ሲባል ሴቷ እንስት በግ ትባላለች
“ባለሟል” የተመረጠና ከፍ ያለ ደረጃ ያለውን ሰው፣ በፖለቲካና በማኅበረ ሰቡ ውስጥ ሁነኛ ቦታ ያለውን ሰው ያመለክታል።
“ባልንፈራ” እንደ ጓደኛ ወይም እንደ የትዳር አጋር ከአንድ ሰው ጋር አብሮ መሆንን ወይም ኅብረት ማድረግን ያመለክታል።
ባሕል የሚያመለክተው ለረጅም ዘመን የተያዘና ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ የኖረ ወግ ወይም ልማድ ነው።
አንድን ሰው ባርያ ማድረግ ያ ሰው ለጌታ እንዲገዛ ማስገደድ ወይም አንድን መግዛት ማለት ነው። ባርነት በሰዎች ወይም በነገሮችና በሁኔታዎች ቁጥጥር ሥር መሆን ማለት ነው።
አገልጋይ በውዴታ ወይም በግዴታ ለሌላው የሚሠራ ሰው ነው። “ባርያ” የሚለው ቃል “አገልጋይ” ማለትም ይሆናል። ከዐውዱ ጋር ይበልጥ የሚስማማው የትኛው ቃል እንደሆነ ብዙ ጊዜ ምንባቡ ግልጽ ያደርጋል
“ባዕድ” ወይም “መጻተኛ” የሚለው ከራሱ አገር ውጪ የሚኖርን ሰው ያመለክታል። በተለይም ብሉይ ኪዳን ውስጥ ከራሱ ሕዝብ መካከል ወጥቶ ሌላ ሕዝብ ጋር የሚኖር ሰው ማለት ነው።
“ባድማ” ወይም “ወና ማድረግ” መኖሪያ የነበረውን ከእንግዲህ መኖሪያ እስከማይሆን ድረስ አንድ ቦታ ማጥፋት መደምሰስ ማለት ነው።
ቤተ መቅደስ እስራኤል ለጸሎትና ለእግዚአብሔር መሥዋዕት ለማቅረብ የሚሰበሰቡበት ዙሪያውን በተከበበ አደባባይ ውስጥ ያለ ሕንፃ ነው። ቤተ መቅደስ የነበረው ኢየሩሳሌም ከተማ ውስጥ ባለው የሞሪያ ተራራ ነበር።
“ቤተ መንግሥት” ከቤተሰቡና ከአገልጋዮቹ ጋር ንጉሥ የሚኖርበት ሕንፃ ወይም ቤት ማለት ነው።
መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቤተሰብ በዚህ ዘመን፣ “የሩቅ” ቤተሰብ የምንለውን ጨምሮ በጋብቻ ወይም በመወለድ የተዛመዱ ሰዎች መኅበረሰብ ነው።
“ቤተ ሰብ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የቤተ ሰብ አባሎችንና ያሉዋቸውን አገልጋዮች ጨምሮ አንድ ቤት ውስጥ አብረው የሚኖሩ ሰዎችን ሁሉ ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙውን ጊዜ፣ “ቤት” ጥቅም ላይ የዋለው በምሳሌያዊ መልኩ ነው።
“ብልሹ” እና፣ “ብልሽት” የሰዎችን ክፋትና ግብረ ገባዊ ዝቅጠት ያመለክታል።
ብልት ወይም ክፍል የአንድ ሕንፃ፣ አካል ወይም ቡድን አንድን ክፍል ያመለክታል።
“ብልጥ” በተለይ ተግባራዊ በሆኑ ነገሮች በጣም ብልህና አስተዋይ ሰው ነው
“ብሔር” አብዛኛውን ጊዜ የሚያመለክተው ከአንድ ቅድመ አባት የተገኙትን ትውልዶችንና ተመሳሳይ ቋንቋና ባሕል ያላቸው ሰዎች ነው።
ብር ሳንቲሞችን፣ ጌጣጌጦችን፣ ዕቃዎችንና ማስዋቢያዎችን ለመሥራት የሚያገለግል አንጸባራቂ ነጭ/ግራጫ መልክ ያለው የከበረ ድንጋይ ነው
መጽሐፍ ቅዱስ “ብርሃን” የሚለውን ቃል በተለያዩ ምሳሌያዊ ገለጻዎች ይጠቀምበታል። ብዙውን ጊዜ ጻድቃን፣ ቅድስናንና እውነትን ለማመልከት እንደ ተለዋጭ ዘይቤ ያገለግላል።
“ብርታት” የሚለው ቃል አካላዊ፣ ስሜታዊ ወይም መንፈሳዊ ጥንካሬን ነው። ማበርታት አንድን ሰው ወይም ነገር ጠንካራ ማድረግ ማለት ነው
“ብቁ” የሚለው ቃል የተወሰኑ ጥቅሞችን ለመቀበል ወይም የተለያዩ ሙያዎች ባለቤት የመሆንን ዕውቅትና ማግኘት ማለት ነው።
ተመስጦ የሚባለው ሰውየው እንቅልፍ ላይ ባይሆንም፣ አንድ ሌላ ነገር እየተመለከተ ወይም እየተለማመደ ከመሆኑ የተነሣ በዙሪያው ስላለው ነገር ግንዛቤ የሚያጣባት የአእምሮ ዝንባሌ ነው።
ተኩላ አደገኛ ሥጋ በል አውሬ ሲሆን፣ ከቀበሮ ጋር ይመሳሰላል።
ሁለቱም ሰራዊት ውስጥ ሆኖ መዋጋትን የሚያመለክቱ በመሆናቸው፣ “ተዋጊ” እና፣ “ወታደር” ትርጕማቸው ተመሳሳይ ነው። ያም ሆኖ ግን፣ መጠነኛ ልዩነትም አላቸው።
“ተገዢ” የሚለው በሌላው ሰው ሥልጣን ሥር መሆንን ያመለክታል፥ “መገዛት” – “ለሌላው ሰው ሥልጣን” ታዛዥ መሆን ማለት ነው
ይህ ቃል የሚያመለክተው ቅንነትን ሲሆን፣ ሰው ባያይ እንኳ በጠንካራ ግብረ ገባዊ መርሕና ፀባይ በመነሣሣት ታማኝ ሆኖ መገኘትን ነው።
“ታጋሽ” እና፣ “ትዕግሥት” የሚለው ቃል አስቸጋሪ የሆነ ሁኔታ መቋቋምን ወይም በዚያ ውስጥ በጽናት መኖርን ያመለክታል። አብዛኛውን ጊዜ ትዕግሥት መጠበቅንም ይጨምራል።
ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “ትልቅ ማድረግ” ታዋቂነት እንዲያገኝ በማሰብ ወደ አንድ ሰው ወይም አንድ ነገር የሌሎችን ትኵረት መሳብ ማለት ነው።
ትውልድ የሚባለው በአንድ ዘመን የተወለደና በአንድ ዘመን የነበረ የሰዎች ስብስብ ነው።
ችጋር በመላው አገር ወይም አካባቢ የምግብ እጥረትን የሚጨምር ጥፋት ሲስፋፋ ማለት ነው።
“ችግር” የሚለው ቃል የሚያመለክተው በጣም አዳጋችና አስጨናቂ የሕይወት ልምምድን ነው። “ሁከት” ከአንዳች ንገር የተነሣ መረበሽ ወይም መጨነቅ ማለት ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ፣ “ኀላፊ” ወይም “ባለ ዐደራ” የሚለው የጌታውን ንብረትና የሥራ እንቅስቃሴን በተመለከተ ሙሉ ኀላፊነት የተሰጠውን አገልጋይ ለማመልከት ነው።
ነቀፋ የአንድን ሰው ፀባይና አኗኗር መብቶች ወይም ይሁንታ መንፈግ ማለት ነው። ብዙውን ጊዜ ነቀፋ ሰውየውን በተመለከተ አሉታዊ ቃል መሰንዘር ነው።
ነብር ጥቁርና ነጭ ዝንጉርጉር መልክ ያለው ትልቅ ድመት መሰል የዱር አውሬ ነው።
ነገድ ብዙውን ጊዜ ከአንድ ቀዳሚ አባት የተገኙ ሰዎች ስብስብ ማለት ነው።
“ነጻ ማድረግ” አንድ ሰው ከተከሰሰበት በደል ወይም ርኩሰት ነጻ መሆኑን በግልጽ መናገር ወይም ማወጅ ማለት ነው።
“ናስ” - መዳብናን ቆሮቆሮን አብሮ በማንጠር የሚሠራ አንድ ዐይነት ብረት መሳይ ነገር ነው። ጥቁር ቡኒ መልክ ቢኖረውም በመጠኑ ወደ ቀይም ወሰድ ያደርገዋል።
ንስር እንደ ዓሣ፣ አይጥ፣ እባብና ጫጩት የመሳሰሉ ትንንሽ እንስሳትን የሚመገብ በጣም ግዙፍና ብርቱ ወፍ ነው።
“ንቀት” አንድ ሰው ለሌላው ሰው ወይም ለሌላው ነገር ክብር መንፈጉን የሚያሳይበት መንገድ ነው። ክብር የተነፈገው፣ “የተናቀ” ይባላል።
“ንብረት ማድረግ” እና፣ “ንብረት” ብዙውን ጊዜ የሚያመለክቱት የአንዳች ነገር ባለቤት መሆንን ነው። አንድን ነገር ወይም አካባቢን መቆጣጠርንም ያመለክታል። አብዛኛውን ጊዜ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ጥቅም ላይ የዋሉት በዚህ መልክ ነው።
ንዴት ከቁጥጥር የወጣ ቁጣ ነው። አንድ ሰው ከተናደደ፣ አጥፊ በሆነ ሁኔታ ቁጣውን እየገለጸ ነው ማለት ነው።
“ንጉሣዊ” የሚለው ቃል ከንጉሥ ወይም ከልዕልት ጋር የተያያዙ ሰዎችንና ነገሮችን ማለትም ዙፋናቸውን፣ ቤተ መንግሥታቸውን፣ ልብሶቻቸውንና ልጆቻቸውን ይመለክታል።
ንጉሥ የአንድ ነጻ ከተማ፣ መንግሥት ወይም አገር መሪ ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “ንሑሕ ያልሆነ” የሚለው ምሳሌያዊ አነጋገር የሚያመለክተው ሕዝቡ ሊነካው፣ ሊበላው ወይም መሥዋዕት ሊያቀርበው እንደማይገባው እግዚአብሔር የተናገረለት ነገርን ነው።
አህያ ከፈረስ የሚያንስና ትላልቅ ጆሮዎች ያሉ ፈረስን የሚመስል ባለ አራት እግር አገልጋይ እንስሳ ነው።
“አለመታዘዝ” ሥልጣን ላይ ያለ ሰው ትእዛዝን ወይም መመሪያን አለመቀበል ማለት ነው። ይህን የሚያደርግ ሰው የማይታዘዝ ይባላል።
“አለቃ” የሚለው ቃል በተወሰኑ አካል ላይ ከፍ ያለ ሥልጣን ያለውን ወይም በጣም አስፈላጊ መሪን ያመለክታል።
“አለ አግባብ” እና፣ “አግባብ ያልሆነ” የተሰኙት ቃሎች ሰዎችን መግፋት፣ ማሳዘን፣ ብዙውን ጊዜ በጣም በሚጎዳ ሁኔት መበደል ማለት ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “አማኝ” ኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝ መሆኑን የሚያምንና የሚደግፍ ማለት ነው
“አሥረኛ” ወይም፣ “አሥራት” የተሰኙት ቃሎች የአንድን ሰው ገንዘብ፣ እህል፣ የቤት እንስሳት ወይም ሌሎች ንብረቶች አንድ አሥረኛ ክፍል ያመለክታል።
እግዚአብሔር ለሙሴ እስራኤል ሊታዘዟቸው የሚገባ ብዙ ትእዛዞች ሰጥቶታል። ከእነዚህ ትእዛዞች አሥሩን በሁለት የድንጋይ ጽላቶች ላይ ጽፏቸዋል።
አሥራ ሁለት የእስራኤል ነገዶች የተባሉት የያዕቆብ ልጆችና የእነርሱ ዘሮች ናቸው።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “አረማዊ” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው ያህዌን ሳይሆን ሐሰተኛ አምላኮችን የሚያመልኩ ሰዎች ለማመልከት ነበር።
“አልፎ መስጠት” (መካድ) ሌላውን ሰው የሚያሳስትና የሚጎዳ ተግባር ነው። “አሳልፎ ሰጪ” (ካጂ) የተማመነበትን ወድጁን አሳልፎ የሚሰጥ ወይም የሚክድ ሰው ነው።
“አስማት” ከእግዚአብሔር ከሚመጣው ውጪ ልዕለ ተፈጥሮአዊ ኀይል መለማመድ ወይም መጠቀም ነው። አስማት የሚለማመድ ሰው አስማተኛ ይባላል።
ቃሉ የሚያማለክተው ገና ከመሆኑ በፊት አንድን ነገር ማወቅን ነው።
አስተማሪ ለሌሎች ሰዎች አዲስ መረጃ የሚሰጥ ሰው ነው። አስተማሪዎች ሰዎች ዕውቀትና ሙያ እንዲያገኙ ይረዳሉ
ቃል በቃል ሲወሰድ አስተምህሮ ትምህርት በተለይም ሃይማኖታዊ ትምህርት ማለት ነው።
“አስተዳደር” እና “አስተዳዳሪ” የተሰኙት ቃሎች የአንድ አገር ሰዎች ሥርዓት ባለው መንገድ እንዲኖሩ መምራትን ወይም ማስተዳደርን ያመለክታል።
ቃል በቃል ከተወሰደ፣ “አባት” የአንድ ሰው ወንዱ ወላጅ ማለት ነው። ይህን ቃል በተመለከተ በርካታ ምሳሌያዊ አነጋገሮች አሉት።
ብሉይ ኪዳን ውስጥ፣ “አባቶች” ለሚለው ቃል የሚያመለክተው የአይሁድ ሕዝቡ መሥራች የሆኑትን አባቶች (ርዕሳነ አበው) በተለይም አብርሃም፣ ይስሐቅንና ያዕቆብን ነው።
አንበሳ እጁ የገባውን የሚገድልበትና የሚግነጣጥልበት ጥርሶችና ጥፍሮች ያሉት ባለ አራት እግር ትልቅ የዱር አውሬ ነው።
“አንበጣ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው አንዳንዴ እጅግ በብዛት የሚመጡ፣ ያገኙትን ሁሉ የሚበሉ በጣም አጥፊ ትልቅ በራሪ ፌንጣዎች ናቸው።
“አንገተ ደንዳና” የሚለው ፈሊጣዊ አነጋገር ለእግዚአብሔር ባለ መታዘዝ የዳኑትንና ተግሣጹን የማይቀበሉ ሰዎችን ያመለክታል። እነዚህ ትዕቢተኞች ናቸው።
አእምሮ የሚያስብና ውሳኔ የሚያደርግ የሰው ተፈጥሮ ክፍል ነው።
አክሊል ንጉሦችና ልዕልታትን የመሳሰሉ መሪዎች ራሳቸው ላይ የሚያደርጉት ክብ ቅርጽ ያለው ጌጥ ነበር። አክሊል መድፋት አንድ ሰው ራስ ላይ አክሊል ማኖር ማለት ሲሆን፣ በምሳሌያዊ ትርጕሙ፣ “ማክበርን” ያመለክታል።
“አክብሮት” ለአንድ ሰው ወይም አንዳች ነገር ጥልቅ ስሜትና ክብር ያመለክታል።
አውራጃ አንድ ወረዳ ወይም የአገር ክፍል ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙውን ጊዜ ስለሌላ “እንስሳ” ለመናገርም ጥቅም ላይ ይውል ነበር
“አዛዥ” የተወሰኑ ወታደሮችን የመምራትና የማዘዝ ኃላፊነት ያለውን የሰራዊት መሪ ያመለክታል።
“አደባባይ” ዙሪያውን የተከበበና ከላይ በኩል ክፍት የሆነ ገላጣ አካባቢ ነው።
“አዲስ ኪዳን” የሚለው አገላለጽ የሚያመለክተው በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ መሥዋዕት በኩል እግዚአብሔር ከሕዝቡ ጋር ያደረገውን ስምምነት ወይም ውል ነው።
“አዲስ ጨረቃ” የሚባለው ጨረቃ በመሬት ምሕዋር ዙሪያ ስትጓዝ የሚኖራት የመጀመሪያው ገጽታዋ ነው። በዚህ ጊዜ ጨረቃ ፍጹም ጨለማ መስላ ትታያለች ወይም ጫፏ ላይ ትንሽ ማጭድ መሰል ቅርጽ ያለው ብርማ ብርሃን ይኖራታል።
አጋዘን ጫካዎች ውስጥ ወይም ተራሮች ላይ የሚኖር ግዙፍና የሚያምር ባለ አራት እግሮች እንስሳ ነው። ወንዱ አጋዘን በጣም ትላልቅ ቀንዶች አሉት።
ቃል በቃል ሲወስድ፣ “አጥፊ” የሚለው ቃል፣ “የሚያጠፋ ሰው” ማለት ነው።
ብዙውን ጊዜ፣ “እህል” የሚያመለክተው እንደ ስንዴ፣ ገብስ፣ በቆሎ፣ ማሽላ ወይም ሩዝን የመሳሰሉ ለምግብ የሚሆኑ እህል ዘሮችን ነው። አንዳንዴ ዘሩ ራሱን ያመለክታል።
“እምነት የሌለው” የማያምን ወይም ማመን የማይፈልግ ማለት ነው።
“እምነት” እኛ “መተማመን” አንድ ነገር እውነት መሆኑንና ያም ነገር በእርግጥ የሚፈጸም መሆኑን እርግጠኛ መሆንን ያመለክታሉ። በድፍረትና በልበ ሙሉነት መንቀሳቀስንም ያመለክታሉ።
እረኛ በጎችንና እነርሱን የመሳሰሉ እንስሳትን የሚጠብቅ ሰው ነው
እርሾ ሊጥ ኩፍ እንዲል የሚያደርግ ነገር ነው። እርሾ የገባበት ሊጥ የቦካ ይባላል።
ብዙውን ጊዜ “ጭፍጨፋ” በአንድ ጊዜ ብዙ እንስሳት ወይም ሰዎችን መግደል ወይም በአሰቃቂ ሁኔታ መግደል ነው። ማረድ በሚለው ቃል ከተጠቀምን ደግሞ ለመብል እንዲሆኑ ጥቂት እንስሳትን መግደልም ይሆናል
እሳት አንድ ነገር ሲቃጠል የሚገኝ ሙቀት፣ ብርሃንና ነበልባል ነው።
እስር ቤት የሚያመለክተው በጥፋታቸው እንዲቀቱ ወንጀለኞች የሚጠበቁበትን ቦታ ነው። እስረኛ እስር ቤት ውስጥ የሚጠበቅ ሰው ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “እስትንፋስ” የሚለው ቃል ብዙውን ጊዜ ሕይወትን ለመስጠት ወይም በሕይወት መሆንን ለማመልከት በምሳሌያዊ መልኩ ጥቅም ላይ ውሏል።
እበት የእንስሳ እዳሪ ሲሆን፣ መሬትን ለማለስለስ ወይም ለማዳበር በሚውልበት ጊዜ ማዳበሪያ ይባላል።
እባብ የዘንዶ ሌላ ስም ነው። በኤደን አትክልት ቦት ከሔውን ጋር በተናገረ ጊዜ ሰይጣን በዚህ ስም ነበር የተጠራው
እኅት የምትባለው ቢያንስ በአንዱ ወላጅ ከሌላው ጋር የምትጋራ እንስት ናት
ብዙውን ጊዜ ብሉይ ኪዳን ውስጥ እግዚአብሔር ስለ ራሱ ሲናገር በተውላጠ ስም ከመጠቀም ይልቅ፣ በራሱ መጠሪያ ስም ይጠቀማል።
“እንከን” ወይም ነውር አንድ እንስሳ ወይም ሰው ላይ ያለ ጉድለትን ወይም ሙሉ ያለመሆንን ያመለክታል። ሰዎች ላይ ያለ በደልን ወይም መንፈሳዊ ጉድለትንም ያመለክታል።
እንደ ራሴ(አምባሳደር)ሀገሩን በይፋ በመወከል ለውጪ አገሮች ጋር ግንኙነት እንዲያደርግ የሚመረጥ ሰው ነው፥ ምሳሌያዊ በሆነ መልኩ ጥቅም ላይ የሚውል ሲሆን አንዳንዴ ጠቅለል ባለ ሁኔታ፣ “ተወካይ” ተብሎም ይተረጎማል።
እንጀራ ውሃና ዘይት ተቀላቅሎ ከተቦካ ዱቄት ሊጥ ይሠራል። ከዚያ ሊጡ የእንጀራውን ወይም የዳቦውን ቅርጽ እንዲይዝ ተደርጎ ይጋገራል።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “እጅ” የሚለው ቃል በምሳሌያዊ አነጋገር በበርካታ ቦታዎች ጥቅም ላይ ውሏል።
“ከንቱ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ምንም ጥቅም ወይም ዓላማ የሌለውን ነገር ነው። ከንቱ ነገሮች ባዶና እርባነ ቢስ ናቸው።
“ከፍታ ቦታዎች” የሚለው ሐረግ የጣዖት አምልኮ መሠዊያና ማምለኪያ ቤት የሚሠራባቸው ኮረብቶች ወይም ተራሮች ላይ ያሉ ቦታዎችን ያመለክታል።
“ከፍታ” እና “በከፍታ” የተሰኙ ቃሎች ሰማይን የሚያመለክቱ ፈሊጣዊ አነጋገር ናቸው።
“ኪሩብ” እና “ኪሩቤል” በመባል በብዙ ቊጥር የሚጠሩት እግዚአብሔር የፈጠራቸው የተለዩ ዓይነት ሰማያዊ አካሎች ናቸው። ኪሩቤል ክንፎችና የእሳት ነበልባል እንዳላቸው መጽሐፍ ቅዱስ ያመለክታል።
ካባ ወንዶችም ሆነ ሴቶች የሚለብሱት እጅጌ ረጃጅም ከውጭ የሚደረብ ልብስ ነው። ከኮት ጋር ይመሳሰላል።
ክራርና መሰንቆ እስራኤላውያን እግዚአብሔርን ለማምለክት የሚጠቀሙባቸው ትናንሽ ባለ ገመድ የሙዚቃ መሣሪያዎች ናቸው።
“ክብር” የሚለው ቃል ብዙ ጊዜ ከሀብትና መልክ ጋር የሚያያዝ የላቀ ውበትና ግርማ ያመለክታል
“ክፉ አድራጊ” ኀጢአትና ዐመጻን የሚያደርጉ ሰዎች አጠቃላይ መገለጫ ነው።
ወራሽ የሚባለው የአንድ የሞተ ሰው ንብረት ወይም ገንዘብ የመቀበል ሕጋዊ ዕውቅና የተሰጠው ሰው ነው።
“ወሬ” አንድን ሁኔታ አስመልክቶ በቃል ወይም በጽሑፍ አንዱ ለሌላው የሚናገረው ነው።
ወርቅ ቢጫ መልክ ያለው በጣም ውድ ነገር ነው። በጥንት ዘመን ወርቅ ከማንኛውም የበለጠ ውድ ነገር ነበር።
መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ጣዖቶች፣ ጌጣጌጦች፣ መሠዊያዎች፣ የቃል ኪዳኑ ታቦት የተወሰነ ክፍልና መገናኛው ድንኳን ወይም ቤተ መቅደሱ ውስጥ የነበሩ ሌሎች ነገሮች የሚሠሩት ከወርቅ ነበር። አንዳንዴ፣ “ወርቅ” የሚባለው ወርቅ የተለበጠ እንጂ እውነተኛ ወርቅ ላይሆን ይችላል። በዚህ ጊዜ፣ “ወርቃማ” ወይም፣ “ወርቅ የተለበጠ” በተሰኙ ሐረጎች እንጠቀማለን።
ወርካ ረጅም፣ ትልቅ ግንድና ጥላ የሚሆኑ ሰፋፊ ቅርንጫፎች ያሉት ዛፍ ነው።
ወሲባዊ እርኩሰት የሚለው ኃረግ በአንድ ወንድ እና ሴት መካከል የከጋብቻ ውጪ የሚፈጸም ወሲብን ያመለክታል። ይህ ከእግዚአብሔር ሕግ ጋር ይቃረናል።
“ወንጀል” ብዙውን ጊዜ የሚያመለክተው የአንድ አገርን ወይም መንግሥትን ሕግ የማፍረስ ኃጢአትን ነው። እንዲህ ያለውን በደል የፈጸመ ሰው ወንጀለኛ ይባላል።
በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት ወይን መርገጫ የወይን ጠጅ ለመሥራት የወይኑ ፍሬ የሚረገጥበት ቦታ ነው።
ወይን ጠጅ ከወይን ፍሬ ጭማቂ የሚሠራ የተብላላ መጠጥ ነው። ያልተብላላው የወይን ፍሬ ጭማቂም በዚሁ ስም ይጠራል።
በብሉይ ኪዳን ዘመን፣ “ወይን ጠጅ ኀላፊ” ለንጉሡ ወይን በጽዋ የሚያቀርብ ሰው ሲሆን፣ ወይኑ ያልተመረዘ መሆኑን ለማረጋገጥ ብዙውን ጊዜ ኀላፊው መጀመሪያ እንዲቀምስ ይደረግ ነበር።
“ወዳጅ” የሚለው ቃል፣ “የሚወድ ሰው” ማለት ሲሆን ብዙውን ጊዜ የሚያመለክተው ግብረ ሥጋዊ ግንኙነት ያላቸው ሰዎችን ነው።
ወገብ በታችኛው ጎድንና በዳሌ አጥንት መካከል የሚገኝ የሰው ወይም የእንስሳ አካል ክፍል ነው፣ አንዳንዴ ታችኛው የሆድ ዕቃም ይባላል።
“ወጥመድ” እና፣ “አሽከላ” የተሰኙት ቃሎች እንስሶችን ለመያዝና ከዚያ እንዳያመልጡ ለመድረግ ጥቅም ላይ የሚውሉ ነገሮች ናቸው። የሚጠመደውን እንስሳ በድንገት እንደያዘው ብዙውን ጊዜ ወጥመዱ ወይም አሽክላው ድብቅ ቦታ ላይ ይቀመጣል
መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ዋሽንት ከአጥንትና ከእንጨት የሚሠራ የሙዚቃ መሣሪያ ሲሆን ድምፅ እንዲያወጣ መተላለፊያዎች ይሠሩለትም ነበር።
ይህ ቃል የሚያመለክተው መልካምም ሆነ ክፉ አንድ ሰው ላደረገው የሚቀበለውን ነገር ነው። “ዋጋ መስጠት” የሚያመለክተው የሚገባውን ነገር ለሰው መስጠትን ነው።
ከመጀመሪያው ትርጕሙ በተጨማሪ፣ “ውሃ” - እንደ ውቅያኖስ፣ ባሕር፣ ሐይቅ ወይም ወንዝን የመሳሰሉ የውሃ አካል ይጨምራል።
“ውድ” የሚለው ቃል በጣም የተወደዱ፣ በጥቂቱ የሚገኙ ወይም ከፍ ያለ ዋጋ ያላቸውን ሰዎች ወይም ነገሮችን ያመለክታል።
“ዐመድ” የሚለው የሚያመለክተው እንጨት ከተቃጠለ በኋላ የሚቀረውን ግራጫ ዱቄት መሳይ ነገርን ነው። ዋጋ ቢስ ውይም ጥቅም የሌለውን ነገር ለማመልከት ምሳሌያዊ በሆን መልኩ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ጥቅም ላይ ውሏል።
የትርጉም ሥራው ፕሮጀክት በሚጠቀምበት ቃል ተጠቀሙ
“ዐምድ” ጣራ ወይም ሌላውን የሕንጻ ክፍል ደግፎ ለመያዝ የሚያገለግል ቀጥ ብሎ የሚቆም ነገር ነው። “ምሰሶ” የዐምድ ሌላ ስም ነው።
ዐዋጅ የሚባለው ሕግን ወይም መምሪያን ለሰዎች በአደባባይ በግልጽ መናገር ነው።
“ዐይነት” እና “ዐይነቶች” የሚባሉት ባሕርያትን በመጋራት የተያያዙ ነገሮች ቡድን ወይም ምድብ ናቸው።
ዓሣ አጥማጆች ለመግብ የሚሆናቸውንና ሸጠው ገንዘብ የሚያገኙበትን ዓሣ ከባሕር የሚያጠምዱ ሰዎች ናቸው። አዲስ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን ዓሣ አጥማጆች ዓሣ የሚያጠምዱት በመረብ አማካይነት ነበር።
ዓሣማ ሰዎች ለምግብነት የሚያረቡት ባለ አራት እግርና ሸኾና ያለው እንስሳ ነበር። ሥጋው የዓሣማ ሥጋ ይባላል።
“ዕረፍት” የሚለው ቃል ዘና ለማለትና ኀይልን ለማደስ የሚሠሩትን ማቆም ማለት ነው።
ዕቁባት ቀድሞውኑ ሚስት ያለችው ወንድ ሁለተኛ ሚስት ናት። ብዙውን ጊዜ ዕቁባት የሰውየው ሕጋዊ ሚስት አትሆን።
ዕቡይ ሰው ከሚገባው በላይ ስለ ራሱ ከፍ ያለ ግምት አለው።
ከ . . . ጋር ግንኙነት፣ ከ . . . ጋር መተኛት፣ አብሮ ተኛ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እነዚህ ቃሎች በተዘዋዋሪ ግብረ ሥጋ ግንኙነት መፈጸምን የሚያመለክቱ ናቸው።
“ትዕቢተኛ” እና፣ “ትዕቢት” ስለ ራሱ ከፍ ያለ ሐሳብ ያለውንና ከሌሎች የበለጠ እንደ ሆነ የሚያስብን ሰው ያመለክታል።
“ዕጣ” አድልዎ የሌለበት ምርጫ ወይም ውሳኔ ለማድረግ ሲታሰብ ሰዎች ምልክት የተደረገባቸው ተመሳሳይ ነገሮችን ይጥላሉ ወይም ከሌሎች ተመሳሳይ ነገሮች መካከል አንዱን ማንሣት ማለት ነው። እግዚአብሔር ምን እንዲያድረርጉ እንደሚፈልግ ማወቅ የሚፈልጉ ሰዎች ብዙውን ጊዜ ዕጣ በመጣል ዕጣ በማውጣት ይጠቀሙ ነበር።
ዕጣን ከዛፍ ሙጫ የሚገኝ ጣፋጭ ሽታ ያለው ቅመም ነው። ሽቱኑ ሌላም ጣፋጭ መዓዛ ያለው ነገር ለመሥራት ያገለግላል።
ነጻ መሆን፣ ነጻነት፣ አርነት “ነጻ መሆን” ወይም፣ “ነጻነት” ባርያ አለመሆንን በምንም ዓይነት ቀንበር ሥር አለመሆንን ያመለክታል።
ዕጣን እሳት ላይ በሚደረግበት ጊዜ ደስ የሚል ሽታ የሚሰጥ ጣፋጭ መዓዛ ያላቸው ቅመሞድ ድብልቅ ነው። እነዚህ ቅመሞች ከዕፅዋት ክፍሎች የተገኙ ሲሆኑ፣ በጣም ጥቃቅን እስኪሆኑ ድረስ ይደቅቃሉ።
ዕፍረት አንድ ሰው ወይም ሌላው ካደረገው መጥፎ ወይም ተገቢ ያልሆነ ነገር የተነሣ የሚደርስ ውርደት ወይም ጥሩ ስሜት እንዳይኖር የሚያደርግ ሕመም ነው
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ዘላለም” የሚያመለክተው ፍጻሜ የሌለውን ጊዜ ነው። አንዳንዴ፣ በታም ረጅም ጊዜን ለማመልከትም ጥቅም ላይ ይውላል።
“ዘመን/ዕድሜ” አንድ ሰው የኖረበት ዓመት ቁጥር ያመለክታል አጠቃላይ በሆነ መልኩ ጊዜን ወይም ወቅትን ያመለክታል።
“ዘመድ” በሥጋና በደም የቅርብ ግንኙነት ያለው ሰው ነው።
መዝራት ተክል ለማግኘት ዘሮችን ምድር ውስጥ ማኖር ማለት ነው። ይህን የሚያደርግ ሰው፣ “ዘሪ” ይባላል
ዘር እርሱን የመሳሰሉ ብዙ ዘሮች እንዲገኙ መሬት ላይ የሚዘራ ወይም የሚተከል የአትክልት ክፍል ነው። በርካታ ምሳሌያዊ ትርጉሞችም አሉት
ዘር (ልጅ) ቀጥተኛ የደምና ሥጋ ዝምድና ያለው ወይም የሩቅ ዘመድ የሆነ ሰው ነው።
“ዘንባባ” ረጃጅም፣ በቀላሉ የሚተጣጠፍ፣ ከጫፉ ጀምሮ እንደማራገቢያ ዓይነት ቅጠል ያበዛባቸው ቅርንጫፎች ያሉት ረጅም የዛፍ ዘር ነው።
ዘይት ከአንዳንድ ተክሎች ወይም ፍሬዎች ሊገኝ የሚችል ወፈር ያለ ፈሳሽ ነገር ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን አብዛኛውን ጊዜ ዘይት የሚገኘው ከወይራ ፍሬዎች ነው።
ዙፋን አብዛኛውን ጊዜ ወሳኝ በሆኑ ጉዳዮች ፍርድ ለመስጠት ንጉሥ የሚቀመጥበት የተለየ ወንበር ነው።
ዙፋን አብዛኛውን ጊዜ ወሳኝ በሆኑ ጉዳዮች ፍርድ ለመስጠት ንጉሥ የሚቀመጥበት የተለየ ወንበር ነው።
“ዜና መዋዕል” የሚለው ቃል በዘመናት ውስጥ በጽሑፍ የሰፈረ ሰነድን ነው።
አንድ ዜጋ በአንድ የተወሰነ አገር ወይም መንግሥት ውስጥ የሚኖር ሰው ነው። በተለይም የዚያ አገር ነዋሪ መሆኑን በልጽ ዕውቅና የተሰጠው ሰውን ያመለክታል።
“ዝሙት አዳሪነት” ወይም፣ “ግልሙትና” ገንዘብ ለማግኘት ወይም፣ ለሃይማኖታዊ ሥርዓት የግብረ ሥጋ ግንኙነትን የሚፈጽም ሰው ያመለክታል። ብዙውን ጊዜ ዝሙት አዳሪዎችና ጋለሞቶች ሴቶች ቢሆኑም፣ አንዳንዴ ወንዶችም ሊሆኑ ይችላሉ።
“ዝቅተኛ” እና፣ “ዝቅተኝነት” የተሰኙት ቃሎች ድህነትን ወይም ዝቅ ያሉ ማንነትና ደረጃን ያመለክታሉ።
“ዝግባ” የሚለው ቃል ቀይ ቡናማ እንጨት ያለው ሾጣጣ ጫፍ ያለውን ግዙፍ ዛፍ ያመለክታል። እንደ ሌሎች ሾጣጣ ዛፎች ሁሉ እንደ መርፌ የሾሉ ቅጠሎች አሉት።
“ሐሰተኛ ምስክር” እና “ጠማማ ምስክር” ሰዎችን ወይም ሁኔታዎችን በተመለከተ እውነቱን የማይናገር ሰው ሲሆን፣ ብዙውን ጊዜ እንዲህ ሲደረግ የሚታየው በመደበኛ ፍርድ ቦታ ነው።
“የሕይወት መጽሐፍ” የሚለው ቃል እርሱ ያዳናቸውንና የዘላለም ሕይወት ያሰጣቸውን ሰዎች ስም የጻፈበትን መዝገብ ያመለክታል።
የመጠጥ ቍርባን ወይን ጠጅ መሠዊያ ላይ ማፍሰስን የሚያካትት ለእግዚአብሔር የሚቀርብ መሥዋዕት ነው። ብዙውን ጊዜ የሚቀርበው ከሚቃጠል መሥዋዕትና ከእህል መሥዋዕት ጋር በአንድነት ነው።
“ቀን” ቃል በቃል 24 ሰዓት ውስጥ ያለው ጊዜ ነው። ምሳሌያዊ ሆነ መንገድም ጥቅም ላይ ይውላል።
“ወር” ሲባል አራት ሳምንት ገደማ ያለው ወቅ ነው። እንደምንጠቀምበት የጊዜ አቆጣጠር (በጨረቃ ወይም በፀሐይ) መሠረት አንድ ወር ውስጥ ያሉ ቀኖች ሊለያዩ ይችላሉ።
ብዙውን ጊዜ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሰዓቱ የሚለው ቃል ብዙውን ጊዜ ጥቅም ላይ የሚውለው አንድ ነገር የተፈጸመበትን ጊዜ ለይቶ ለመናገር ነው።
ሳምንት ሰባት ቀኖች ያሉት ጊዜ ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን፣ “ትጋት” ይባል የነበረው አንድ የከተማ ጠባቂ ወይም ዘበኛ ጠላት ከሚሰነዝረው የትኛውም ጥቃት ለመጠበቅ ግዳጅ ላይ የሚሆንበት የሌሊቱ ጊዜ ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ቃል በቃል ጥቅም ላይ ከዋለ፣ “ዓመት” 354 ቀኖች የያዙ ጊዜን ያመለክታል። ይህ ጨረቃ በምድር ዙሪያ ለመዞር የሚወስድባትን ጊዜ መጸት እንደማይደርገው እንደ ጨረቃ አቆጣጠር ነው።
“የሚቃጠል መሥዋዕት” የሚባለው መሠዊያው ላይ በእሳት ተቃጥሎ ለእግዚአብሔር የሚቀርብ መሥዋዕት ዐይነት ነው። የሚቃጠለው ለሕዝቡ ኀጢአት ስርየት ለመሆን ነው። “በእሳት መሠዋት” ተብሎም ይጠራል።
“የሚያሰክር መጠጥ” የሚለው ቃል፣ የተብላሉ መጠጦችን ያመለክታል፣ “አልኮል” መጠጥም ይባላል
«የሚያስደስ ነገር» ማለት ሰውን በእጅጉ የሚያስደት ወይንም በዙ ሐሴትን የሚያመጣ ነገር ማለት ነው በ አንድ ነገር መደሰት ማለት
የማኅፀን ፍሬ በሥጋና በደም ከሰዎች ወይም ከእንስሳት ለሚወዱ ሁሉ የሚሰጥ አጠቃላይ ቃል ነው።
“የማይጠቅም” አንዳች ጠቀሜታ የሌለው ማለት ነው።
“የምግብ ቁርባን” የሚባለው ለእግዚአብሔር መሥዋዕት የሚቀርብ እህል ወይም እንጀራ ነው።
“ምጥ” ላይ ያለች ሴት ልጅ ከመውለዷ በፊት ሕመም ይደርስባታል፤ ይህም “የምጥ ጣር” ይባላል።
የራስ ቅል የአንድ ሰው ራስ አጥንት የሆነው ክፍል ነው
እግዚአብሔር በሲና ተራራ ሕጉን በሰጠ ጊዜ የስብሰባ ድንኳን እንዲሠሩ ለእስራኤላውያን ተናግሮ ነበር። ይህ ከእነርሱ ጋር የሚገናኝበት የተቀደሰ ቦታ ነበር። በምድረ በዳ በሚጓዙበት ጊዜ ይዘውት ይሄዱ ነበር፤ እግዚአብሔር ሲነግራቸው መልሰው ይተክሉት ነበር። * የስብሰባው ድንኳን የእንጨት ማዕቀፎች ላይ በተዘረጋ ጨርቅ የተሠራ ቤት ነበር።
የበላይ ተማልካች የሚለው ሐረግ የሚያመለክተው የሌሎች ሰዎች መብትና ጥቅም መከበሩን የመቆጣጠር ሥራ በኅላፊነት የሚከታተል ሰው ነው።
“በደል” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኀጢአት ማድረግን ወይም ወንጀል መፈጸምን ነው።
የበጎ ፈቃድ ስጦታ ማለት የአይሁድ ሕግ ከሚጠይቀው መሥዋዕት የበለጠ ወይም ያለፈ መሥዋዕት ማለት ነው።
የፈቃደኝነት መሥዋዕት ማለትበሙሴ ሕግ ያልተጠየቀ የመሥዋዕት አይነት ነው። የበጎ ፈቃድ ስጦታ ማለት የአይሁድ ሕግ ከሚጠይቀው መሥዋዕት የበለጠ ወይም ያለፈ መሥዋዕት ማለት ነው።
“የባሕር አውሬ” ውቅያኖስ ወለል ላይ ያሉትን የባሕር ሣሮችንና ተክሎችን የሚበላ ግዙፍ የባሕር እንስሳ ነው
“የቤት እንስሶች” የሚባሉት ምግብና ሌሎችም ጠቃሚ ነገሮች ለማግኘት ሰፈር ውስጥ የሚያድጉ እንስሳት ናቸው።
ማቴዎስ በሚያቀርበው የክርስቶስ ልደት ታሪክ መሠረት እነዚህ፣ “የተማሩ” ወይም፣ “ያወቁ” ሰዎች ኢየሱስ በቤተ ልሔም በተወለደ ጊዜ እዚያ ድረስ ስጦታዎች ያመጡለት “ጠቢብባን ሰዎች” ነበር። ምናልባትም ከዋክብትን የሚያጠኑ ኮከብ ቆጣሪዎች ለሆኑ ይችላሉ።
“የተቀደሰ” የሚለው ቃል ቅዱስ የሆነና ለእግዚአብሔር ክብር የተለየ ነገርን ያመለክታል
“የተጠላ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የማይወደድና የተናቀ ነገር ነው። አንድን ነገር “መጥላት” ያንን ነገር አጥብቆ አለመውደድ ማለት ነው።
“እንደ ተጻፈ” ወይም፣ “የተጻፈው” የተሰኙት ቃሎች አዲስ ኪዳን ውስጥ ተደጋግመው ጥቅም ላይ ውለዋል፣ ብዙውን ጊዜ የሚያመለክቱት በዕብራውያን ቅዱሳት መጻሕፍት የተጻፉ ትእዛዞች ወይም ትንቢቶች ነው።
“የኅብረት መሥዋዕት” እስራኤላውያን ለእግዚአብሔር እንዲያቀርቡ ከታዘዙት በርካታ የመሥዋዕት ስጦታዎች አንዱ ነበር። “የምስጋና መሥዋዕት” ወይም፣ “የሰላም መሥዋዕት” ተብሎም ይጠራል።
የኅብረት መሥዋዕት ብሉይ ኪዳን ውስጥ የሰላም መሥዋዕት ተብሎ ይጠራል። ተባዕት ወይም እንስት እንስሳ መሥዋዕት የሚቀርብበት ነው።
የኅጢአት መሥዋዕት ለተፈጸመው ኅጢአት ይቅርታ ለማግኘት ይቀርብ የነበረ መሥዋዕት ነበር
የአይሁድ መሪዎች ካህናትንና የሕግ ምሑራንን የመሳሰሉ የሃይማኖት መሪዎች ነበሩ።
የእህል ቍርባን የሚባለው ብዙውን ጊዜ ከሚቃጠል መሥዋዕት በኋላ ለእግዚአብሔር የሚቀርበውን የስንዴ ወይም የገብስ ዱቄት ነው።
“የእውነት ቃል” የእግዚአብሔር ቃል ወይም ትምህርት ሌላ መጠሪያ ነው።
“የእግር መረገጫ” አንድ ሰው እግሮቹን በተለይም በሚቀመጥ ጊዜ እግሮቹን የሚያሳርፍበት ነገር ነው። መገዛትንና ዝቅ ያለ ማንነትን የሚያመለክት ትርጕም ያለው ምሳሌያው ቃልም ነው።
ኢየሱስ በዚህ ምድር በነበረ ጊዜ የካህናት አለቆች ከፍ ያለ ሥልጣን የነበራቸው የአይሁድ ሃይማኖት መሪዎች ነበሩ።
የወይራ ፍሬ ከወይራ ዛፍ የሚገኝ ትንሽ ሾጣጣ ቅርጽ ያለው ፍሬ ሲሆን፣ አብዛኛውን ጊዜ የሚገኘው በሜድትራኒያን ባሕር አካባቢዎች ነው።
የወይን እርሻ ወይም ልማት ወይን የሚበቅልበት ወይን፣ በእንክብካቤ የሚያድግበት ቦታ ነው።
“የወይን ዛፍ” ወይን የሚያፈራ የዛፍ ዓይነት ነው።
ወይን ፍሬ የወይን ሐረጉ እዚህና እዚያ ተበታትነው የሚያድጉ ትናንሽ ክብ ፍሬዎች ናቸው። ወይን ጠጅ የሚሆነው እነዚህ ፍሬዎች ተጨምቀው ነው።
“የዋህ” የሚለው ቃል ጨዋ፣ እሺ ባይና መከራን በትዕግሥት የሚቀበልን ሰው ያመለክታል። መናደድ ኀይል መጠቀም ተገቢ መስሎ ቢታይ እንኳ ጨዋ ሆኖ ለመገኘት የዋህነት ታላቅ ችሎታ ነው።
“የደም መፍሰስ” በግድያ፣ በጦርነት ወይም በሌላ አደጋ የሰዎችን ሞት ያመለክታል።
የገሊላ ባሕር ምሥራቃዊ እስራኤል ያለ ሐይቅ ነው። የገሊላ ባሕር በዮርዳኖስ ወንዝ ውስጥ ወደ ደቡብ ከዚያም ወደ ሙት ባሕር ይፈስሳል።
“የግብረ ሥጋ ኅጢአት” የሚባለው በወንድና በሴት መካከል ካለው ጋብቻ ውጪ የሚደረግ ማንኛውም የግብረ ሥጋ ግንኙነት ነው። እንዲህ ያለው ከእግዚአብሔር ዕቅድ ውጪ ነው።
“ያልተገረዘ” እና “አለመገረዝ” አካላዊ ግርዘት ያላደረገ ወንድን ያመለክታል። ይህ ቃል በምሳሌያዊ አንጋገርም ጥቅም ላይ ይውላል።
“ያልተፈቀደ” ነገር የሚያደርግ ሰው ሕግ ያፈርሳል።
“ያልታመነ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው እንዲያደርግ እግዚአብሔር ያዘዘውን ነገር የማያደርገውን ሰው ነው። እንዲህ ማድረግ አለመታመን ነው።
የአይሁድ ሕዝብ የሚለማመደውን ሃይማኖት ማለትም የአይሁድ ሃይማኖትን ለማመልከት አዲስ ኪዳን ከተጻፈበት ዘመን አንስቶ እስከዚህ ዘመን ድረስ፣ “ይሁዲ” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ ውሏል።
ደስታ የደስታ ስሜት ወይም ከእግዚአብሔር የሚመጣ ጥልቅ ርካታ ነው። ከዚሁ ጋር ታያያዥ የሆነው፣ “ደስተኛ” የሚለው ቃል በጣም ደስ የተሰኘ ሰውን ያመለክታል።
ደብዳቤ ብዙ ጊዜ ከጸሐፊው ርቀው ላሉ ወገኖች ወይም ሰዎች የሚላክ መልእክት ነው። መልእክት የተለየ ዐይነት ደብዳቤ ሲሆን፣ ብዙውን ጊዜ የሚጻፈው ማስተማርን ለመሰሉ የተለዩ ዓላማ ነው።
“ደጃፍ” የሚባለው የበር ታችኛው ክፍል ነው። ወደ አንድ ቤት ሲገባ ደጃፉን መርገጥ ይገባል።
ይህ ከደጋን ገመድ ቀስትን ማስፈንጠርን የሚያካትት መሣሪያ ዐይነት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ጠላትን ለማጥቃት ወይም ለምግብ የሚሆን እንስሳን ለመግደል ያገለግል ነበር።
እነዚህ ቃሎች አስቸጋሪና አደገኛ ቢሆን እንኳ እውነትን ለመናገርና ትክክለኛውን ለማድረግ ደፋርና ጎበዝ መሆንን ነው የሚያመለክቱት።
አስተዳደራዊ፣ ሕጋዊ ወይም መንፈሳዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ትክክልና ስሕተት የሆኑ ነገሮችን የሚወስን ሰው ዳኛ ወይም ፈራጅ ይባላል።
አንድ ሰው ሲናገር ድምፅ ይጠቀማል፤ ስለዚህም ብዙ ጊዜ “ድምፅ” ንግግርን ወይም ሐሳብ ማስተላለፍን ለማመልከት ጥቅም ላይ ይውላል።
ድብ ጥቁር ቡናማ ጠጉርና ጠንካራ ጥርሶችና ጥፍሮች ያሉት ባለአራት እግር ግዙፍ እንስሳ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ድብ በእስራኤል በብዛት ይገኝ ነበር
“ድነት” የሚለው ቃል ከክፉና ከአደጋ መዳንና ማምለጥን ያመለክታል
ድንኳን ተንቀሳቃሽ መጠለያ ሲሆን፣ የሚሠራው ምሰሶዎች ላይ በማንጠልጠሉና ከእንርሱ ጋር በተያያዙ ጠንካራ ጨርቅ ነበር።
ይህ ቃል የሚያመለክተው ከሰማይ የሚወርድ ጠጣር ነገርን ነው።
ድንግል የግብረ ሥጋ ግንኙነት ያላደረገች ሴት ናት።
“ደኝ” ቢጫ መልክ ያለው ንጥረ ነገር ሲሆን፣ እሳትን በማቀጣጠልም ይረዳል
“ድፍረት” አስቸጋሪ፣ አስፈሪ ወይም አደገኛ ነገሮችን በጉብዝና መጋፈጥ ወይም አንድ ነገር ማድረግ ማለት ነው።
ደረቅ የእህል ዘር መከላከያ ሽፋን ነው። ገለባ ለምግብነት አይጠቅምም፤ ስለዚህም ከእህሉ እንዲለያይ ይደረግና በኋላ ይጣላል።
“ገብስ” እንጀራ ወይም ዳቦ ለማዘጋጀት የሚጠቅም የእህል አይነት ነው
ገዢ፣ አገርን፣ አካባቢን ወይም ክልልን የሚገዛ ሰው ነው። “መግዛት” ሰዎችን ወይም ነገሮችን መምራት ወይም ማስተዳደር ማለት ነው።
ገዢ እንደ አገር መሪ፣ መንግሥት ወይም ሃይማኖታዊ ድርጅት ላይ ሥልጣን ያለውን ሰው የሚያመለክት አጠቃላይ ቃል ነው
“ጉቦ” ወይም መማለጃ፣ ትክክል ወይም ተገቢ ያልሆነ ነገር እንዲያደርግ እዚያ ሰው ላይ ተጽዕኖ ለማሳደር ገንዘብን የመሰለ አንዳች ዋጋ ያለው ነገር መስጠት ማለት ነው።
ጉድጓድ ወደ መሬት በጣም ዝቅ ብሎ የተቆፈረ ድንጋይ ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን፣ “ጉድጓድ” እና “ውሃ መያዣ” ሁለት የተለያዩ የውሃ መገኛ ቦታዎችን ነበር የሚያመለክተው።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ጊዜ” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው የተወሰኑ ነገሮች የተፈጸሙበትን ወቅት ወይም ዘመን ለማመልከት ነው። “ዕድም” ወይም፣ “ዘመን” ወይም “ወቅት” ጋር የሚመሳሰል ትርጕም አለው።
ጊደር ገና ያልወለደች ወጣት ላም ናት። ወራሽ ወራዕ የሚባለው የአንድ የሞተ ሰው ንብረት ወይም ገንዘብ የመቀበል ሕጋዊ ዕውቅና የተሰጠው ሰው ነው።
ጋሻ ከሚወረወር ፍላጻና ከሌሎችም ጠላት ከሚሰነዝራቸው ጥቃቶች ራሱን ለመከላከል አንድ ወታደር በጦርነት ይይዘው የነበረ ነገር ነበር ለአንድ ሰው ጋሻ መሆን እርሱን ከአደጋ መከለከል ማለት ነው
ጌታ የሚለው ቃል ሰዎች ላይ ባለቤትነት ወይም ሥልጣን ያለውን ሰው ያመለክታል።
ግመል ጀርባው ላይ አንድ ወይም ሁለት ሻኛ ያለው ግዙፍ ባለ አራት እግር እንስሳ ነው።
“ግራር” የተሰኘው ቃል በጥንት ዘመን በከነዓን ምድር ይበቅል የነበረው በብዛት ይገኝ የነበረው ቁጥቋጦ ወይም ዛፍ ስም ነው። ዛሬም ቢሆን በዚያ አካባቢ በብዛት ይገኛል።
ግብር ከለላ ለማግኘትና በሕዝቦቻቸው መካከል መልካም ግንኙነት እንዲኖር አንድ መንግሥት ወይም ገዢ ለሌላው የሚያቀርበው ስጦታ ነው።
ብዙውን ጊዜ ግብዣ የተለያዩ የምግብ ዓይነቶች የሚቀርቡበት ታዋቂ ሰፊ ድግስ ነው
ግዙፍ የሚለው ቃል ብዙውን ጊዜ የሚያመለክተው ያልተለመደ ቁመትና ጉልበት ያለውን ሰው ነው።
አብዛኛውን ጊዜ ጎረቤት የሚባለው በአካባቢው የሚኖር ሰው ነው። ይበልጥ አጠቃላይ በሆነ መልኩ፣ በምትኖሩበት ማኅበረ ሰብ ወይም የሰዎች ስብስብ ውስጥ የሚኖር ሰውን ያመለክታል።
ብዙውን ጊዜ ጎርፍ የሚባለው ምድሩን ሁሉ የሚሸፍን ብዛት ያለው ውሃ ነው። የአንድን ነገር ብዛት ወይም በድንገት ነገር ለማመልከትም ምሳሌያው በሆነ መልኩ ጥቅም ላይ ይውላል።
“ጎሳ” ከአንድ አባት የተገኙ ረጅም ሐረግ ያለው ቤተ ሰብ አካሎች ናቸው።
“ጎተራ” ምግብ ወይም ሌሎች ነገሮችን ለማከማቸት የሚያገለግል ማስቀመጫ ነው
“ጠላት/ባለጋራ” አንዳንድ ሰው ወይም አንድን ነገር የሚቃወም ሰው ወይም ሰዎች ማለት ነው።
“ጠማማ” ግብረ ገባዊ ወልጋዳነት ወይም ገዳዳነት ያለውን ሰው ወይም ተግባር ለሚመለከት ጥቅም ላይ የሚውል ቃል ነው። “የተጣመመ” - ወልጋዳ ማለት ነው።
“ጠባቂ” አንድ ነገር በጥንቃቄ የሚመለከት፣ ረጋ ብሎና ቀረብ ብሎ በማስተዋል የሚመረምር ማለት ነው። ቃሉ በርካታ ምሳሌያዊ ትርጕሞችም አሉት።
ጠብ በሰዎች መካከል ያለ አካላዊ ወይም ስሜታዊ ግጭት ማለት ነው
“ጠንቃቃ” የሚለው ቃል ስለሚሠራው ነገር ረጋ ብሎ የሚያስብና ትክክለኛ ውሳኔ የሚያደርግ ሰውን ይገልጣል።
“ጠንካራ” የሚለው ቃል እንደ ዐውዱ ሁኔታ የተለያዩ ትርጕሞች ይኖሩታል። ብዙዎን ጊዜ የሚያመለክተው አስቸጋሪ፣ አዳጋች ወይም የማይበገር ነገርን ነው።
“ጠቢብ” የሚለው ቃል መልካምና ግብረ ገባዊ ነገሮችን የሚረዳና በተረዳው መሠረት የሚኖር ሰው ነው። እውነትና ግብረ ገባዊ የሆኑ ነገሮችን መረዳት፣ “ጥበብ” ይባላል።
ጣዖት እርሱን ለማምለክ ሰዎች የሚያበጁት ነገር ነው። ከአንዱ እውነተኛ አምላክ ይልቅ ለአንዳች ሌላ ነገር ክብር ሲሰጥ ያ ጣዖት አምልኮ ይባላል።
ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “ጥላ” ብርሃን ሲጋረድ የሚፈጠረውን ጨለማ ያመለክታል። በርካታ ምሳሌያዊ ጠቀሜታዎችም አሉት
“ጥልቅ/ጥልቁ”የሚለው ቃል በጣም ሰፊና ጥልቅ ጉድጓድን ወይም ማለቂያ የሌለው ሸለቆን ያመለክታል
ጥሩር የሚባለው በጦርነት ጊዜ ወታደሩን ለመከለል ደረትን የሚሸፍን መሥራሪያ ነው። እስራኤላዊው ሊቀ ካህን ይለብስ የነበረው ልዩ ዐይነት ልብስ ክፍል ጥሩር ይባል ነበር።
ጥርስ ማፋጨት ማለት ጥርሶችን በማያያዝ ወደ ፊት ወደ ኋላ በማድረግ ወይም ግራና ቀኝ በማድረግ እርስ በርሳቸው እንዲፋጩ ማድረግ ማለት ነው። ይህ ብዙውን ጊዜ የሚያሳየው ከባድ ስቃይን (ሕመምን) ወይም ቊጣን ነው።
በጥንት ዘመን ጥቅልል ከአንድ ረጅም የፓፒረስ ገጽ ወይም ከቆዳ የሚሠራ የመጽሐፍ ዓይነት ነበር። ጥቅልሉ ላይ ከተጻፈ ወይም ከተነበበ በኋላ ሰዎች ጫፉ ላይ ትንሽ በትር መሳይ ነገር በማኖር ይጠቀልሉት ነበር
በአጠቃላይ “ጠቃሚ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የሚገኝ መልካም ነገርን ነው። ለራሱ መልካምነገር የሚያስገኝ ወይም ለሌሎች መልካም ነገር የሚያስገኝ ከሆነ አንድ ነገር ጠቃሚ ነው ይባላል።
ጥድ ዓመቱን ሙሉ አረንጓዴ የሆነ፣ ዘሩን የሚይዝበት ሾጣጣ መያዣዎች ያሉት የዛፍ ዓይነት ነው።
ጥፋት የሚለው ቃል ምንም ይግባኝ ወይም ማምለጫ የሌለው ፍርድና ኩነኔን ያመለክታል።
ጦር በአንድ በኩል ሹል ብረት ያለው ሆኖ ጠላት ላይ የሚወረወር ረጅም እጀታ ያለው መሣሪያ ነው
ቃል በቃል፣ “ጨለማ” የብርሃን አለመኖር ማለት ነው። ይህ ቃል የተለያዩ ምሳሌያዊ ትርጕሞችም አሉት።
“ጽድቅ የሌለበት” ኀጢአተኛና ምግባረ ምልሹ ማለት ሲሆን፣ “ኀጥእ” ኀጢአት ማድረግን ወይም፣ ኀጢአተኛ መሆንን ያመለክታል።
“ጽድቅ የሌለበት” ኀጢአተኛና ምግባረ ምልሹ ማለት ሲሆን፣ “ኀጥእ” ኀጢአት ማድረግን ወይም፣ ኀጢአተኛ መሆንን ያመለክታል።
“ጽድቅ የሌለበት” ኀጢአተኛና ምግባረ ምልሹ ማለት ሲሆን፣ “ኀጥእ” ኀጢአት ማድረግን ወይም፣ ኀጢአተኛ መሆንን ያመለክታል።
መጾም ምግብን ወይም አንዳንድ የምግብ ዐይነቶችንና መጠጦችን ለተወሰነ ጊዜ ማቆም ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን “ፈረሰኛ” የሚባለው ብዙውን ጊዜ ፈረስ ላይ ሆኖ ወደ ጦርነት የሚሄድ ሰው ነበር።
ፈረስ ግዙፍ ባለ አራት እግር እንስሳ ሲሆን፣ መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን በአብዛኛው ለእርሻ ሥራና ለሰዎች መጓጓዣ ያገለግል ነበር።
ፈራጅ ሕግን በሚመለከቱ ጉዳዮች የመዳኘትና የመወሰን ሥልጣን እንዲኖረው የተሾመ ባለ ሥልጣን ነው።
“ፊት” የሚለው ቃል የአንድ ሰው ራሱ ከፊት በኩል ያለውን ክፍል ነው፤ ቃሉ አያሌ ምሳሌያዊ ትርጉሞች አሉት።
ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “ፍሬ” የሚበላ የተክል ክፍል ነው። “ፍሬያማ” ብዙ ፍሬ ያለው ማለት ነው። እነዚህ ቃሎች ምሳሌያዊ በሆነ ንግግር ውስጥ ጥቅም ላይ ይውላሉ።
ፍትወት በጣም የጋለ ምኞት ሲሆን፣ ብዙውን ጊዜ ኀጢአት ወይም ግብረ ገባዊ ካልሆነ ነገር ፍላጎት ጋር ይያያዛል።
ፍየል መጠነኛ ቁመት ያለው፣ ከበግ ጋር የሚመሳሰልና በዋነኛነት ደረጃ ወተትና ሥጋ ለማግኘት ሰዎች የሚያረቡት ባለ አራት እግር እንስሳ ነው። የፍየል ግልገል “ወጠጤ” ይባላል።
“ፍጡር” ሰዎችንና እንስሳትን ጨምሮ እግዚአብሔር የፈጠረውን ሕያው ነገር ሁሉ ያመለክታል።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “ፍጹም” የሚለው ቃል በክርስትና ሕይወታችን አስተዋዮችን በሳሎች ሆኖ መገኘትን ነው። አንዳንዴ “ፍጹም” የሚለው ቃል የተሟላና እንከን የሌለበት እስኪሆን ድረስ በክርስትና ሕይወት ማደግ ማለትም ይሆናል።