ወደ ግብጽ መጓዝ ወደ ላይ ወደ ተስፋይቱ ምድር የመጓዝ ተጻራሪ ወደ ታች መውረድ ተደርጐ ይቆጠራል ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መንገድ ሊገለጽ ይችላል:: አት “እስማኤላዊያን ዮሴፍን ወደ ግብጽ ወሰዱት” (ፈሊጣዊ አነጋገርና ተሻጋሪ ግሥ እና የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)
ይህ እግዚአብሔር ዮሴፍን ረድቶታል ሁልጊዜም ከእርሱ ጋር ነበር ማለት ነው:: አት “እግዚአብሔር ዮሴፍን መራው አገዘውም” (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)
እዚህ ጸሓፊው በአሳዳሪው ቤት መሥራቱን በአሳዳሪው ቤት እንደመኖር ይናገራል:: በአሳዳሪዎቻቸው ቤት መሥራት የሚችሉት በጣም ታማኝ የሆኑ ሎሌዎች ብቻ ናቸው፡፡ አት እርሱም በቤት ውስጥ ይሠራ ነበር (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
አሳዳሪው እግዚአብሔር እርሱን እየረዳ እንደሆነ አየ ማለት ነው አት እግዚአብሔር እየረዳው እንደሆነ አሳዳሪው አየ (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)
እግዚአብሔር ዮሴፍ የሚሠራው ሁሉ መከናወንለት አደረገ
ሞገስ ማግኘት በአንድ ሰው ተቀባይነትን ማስረገጥ ማለት ነው በእርሱ ዘንድ የሚለው ፈሊጣዊ አባባል በሰውዬው አመለካከት እንደሆነ ያመለክታል:: ተገቢ ትርጉሞች እነሆ 1) ጲጥፋራ በዮሴፍ ተደስቶአል 2) እግዚአብሔር በዮሴፍ ተደስቶአል (ፈሊጣዊ አባባል ይመልከቱ)
የጲጥፋራ የግል ሎሌው ነበር ማለት ነው
ጲጥፋራ በቤቱና የጲጥፋራ በሆነው ሁሉ ላይ ለዮሴፍ በኃላፊነት ሰጠው
አንድ ነገር በአንድ ሰው ኃላፊነት ሥር ሲሆን ያ ሰው ያንን ነገር ለመንከባከብና ደኀንነቱን ለመጠበቅ ኃላፊነት አለው ማለት ነው:: አት “ዮሴፍ እንዲንከባከብ ሰጠው” (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ተውላጤ ስሞችን ከመጠቀምዎ በፊት “ዮሴፍ” እና “ግብጻዊው” የሚሉ ቃላትን መጠቀም ይችላሉ:: ግብጻዊው ዮሴፍን በቤቱና ባለው ሀብት ሁሉ ላይ ኃላፊነት ሰጠው እናም ከጊዜ ወደ ጊዜ በዮሴፍ ምክንያት እግዚአብሔር የግብጻዊውን ቤት ባረከ::
እነዚህ ሁለቱ ጥቅሶች ለሚቀጥለው ክስተት ዳራ መረጃ እንደሆኑ ለአንባቢያን ለመናገር ይህ ሀረግ ተጠቅሞአል
ጲጥፋራ ዮሴፍን በቤቱና ባለው ተብት ሁሉ ላይ ሾመው
በሚባረከው ነገር ወይም ሰው መልካም ወይም ጠቃሚ ነገር እንዲደረግ ምክንያት መሆን ማለት ነው
እዚህ ጸሐፊው እግዚአብሔር የሰጠውን በረከት በአንድ ነገር ላይ እንደተቀመጠ መሸፈኛ አድርጐ ይናገራል:: አት: “እግዚአብሔር ባረከ” ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ
ይህ ቤት እረሻውንና ከብቶችን ያለመክታል የዚህ ሙሉ ትርጉም ግልጽ ሊደረግ ይችላል:: አት “በጲጥፋራ ቤትና በከብቶችና እርሻው ሁሉ” (ግምታዊ እውቀትና ጥልቀ መረጃ ይመልከቱ)
አንድ ነገር በአንድ ሰው ቁጥጥር ሥር ሲሆን ያ ሰው ሊጠብቀውና ሊንከባከበው ኃላፊነት አለው ማለት ነው አት: “ስለዚህ ጲጥፋራ ባለው ሁሉ ላይ ለዮሴፍ ስልጣን ሰጠው”
ምን ምግብ መመገብ እንዳለበት ከመወሰን በቀር በቤቱ ስላለው ማንኛውም ነገር አይጨነቅም ነበር ይህ በአዎንታዊ መንገድ ሊገለጽ ይችላል አት ጲጥፋራ ምን መመገብ እንደሚፈልግ ብቻ ማሰብ ነበረበት በቤቱ ስላለው ማንኛውም ነገር መጨነቅ የለበትም (ግምታዊ እውቀትና ጥልቀ መረጃ ይመልከቱ)
“አሁንም” የሚለው ቃል ስለ ዮሴፍ ዳራ መረጃ ለመስጠት በታሪኩ መስመር ውስጥ ጣልቃ ማስገባቱን ያመለክታል (ዳራ መረጃ ይመልከቱ)
ሁለቱም ቃላት ተመሣሣይ ትርጉም አላቸው ዮሴፍ የሚያስደስት ቁመና እንዳለው ያመለክታሉ:: ጠንካራና ጥሩ ቁመና ነበረው:: አት: “ጠንካራና መልከመልካም ነበር”
እናም ደግሞ ይህ ሀረግ አድስ ክስተት መጀመሩን ሊያመለክት ተጠቅሞአል (አዲስ ክስተት ማታወቅ ይመልከቱ)
ስሚው ዮሴፍ የጲጥፋራን ሚስት መስብ/ትኩረት ለማግኘት ይህን ቃል ተጠቅሞአል
“ጌታዬ በኃላፊነቴ ሥር ስላለው ስለቤቱ ሁሉ ምንም የሚያውቀው ነገር የለም”:: ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል:: አት “ጌታዬ ስለቤቱ ያምነኛል” (ድርብ አሉታዊነት ይመልከቱ)
አንድ ነገር “በአንድ ሰው ኃላፊነት ሥር” ሲሆን ያ ሰው እንዲንከባከበውና እንዲጠብቀው ኃላፊነት አለው ማለት ነው:: አት፡ “ያለውን ሁሉ በኃላፊነት ስለሰጠኝ” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
እዚህ ጸሓፊው ኃላፊነትን እንደ ትልቅነት ይናገራል አት: “ከማንም ሰው የበለጠ ለዚህ ቤት ኃላፊነት አለኝ” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ይህ በአዎንታዊ መንገድ ሊገለጽ ይችላል:: አት: “እርሱ ያለሰጠኝ ነገር ቢኖር አንቺን ብቻ ነው” (አሉታዊነትን በአዎንታዊነት የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
ዮሴፍ ትኩረት ለመስጠት ጥያቄ ይጠቀማል ይህ በዐረፍተ ነገር መልክ ሊገለጽ ይችላል አት ይህን ክፉ ድርጊት ፈጽሜ በእግዚአብሔር ፊት ኃጢአት አልሠራም (አግናኝ ጥያቄዎችን ይመልከቱ)
ከእርስዋ ጋር እንዲተኛ በተደጋጋሚ ትጠይቀው ነበር ማለት ነው:: የዚህ ጥቅስ ሙሉ ትርጉሙ ግልጽ ሊደረግ ይችላል:: አት: “ዮሴፍ ከእርስዋ ጋር እንዲተኛ ትጐተጉተው ነበር” (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)
እንዲቀርባት
“እንዲሁም ደግሞ” የሚለው ሀረግ በታሪኩ አድስ ክስተት መጀመሩን ለማመልከት ነው (አዲስ ክስተት ስለማታወቅ ይመልከቱ)
በቤቱ ከሚያገለግሉ ሰዎች ማንም
“እናም ወዲያው ሮጦ ወደ ውጪ ወጣ” ወይም “እናም ወዲያው ሮጦ ከቤት ወጣ”
ከዚያም …. ጠራች እንዲህም ሆነ የሚለው ሀረግ በታሪኩ ሁለተኛውን ክስተት ለማመልከት ተጠቅሞአል (አዲስ ክስተት ስለማስታወቅ ይመልከቱ)
ወዲያው ሮጦ ከቤት ወጣ
በቤትዋ የሚሠሩ ሰዎች
“ተመልከቱ” ወይም “ሰማችሁ” ወይም “ስለሚናገረው ነገር ትኩረት አድርጉ”
እዚህ የጲጥፋራ ሚስት ዮሴፍ ሊይዛትና ከእርስዋ ጋር ሊተኛ እንደሞከረ ትከሳለች
ድምጼን ከፍ አድርጌ መጮሄን ሲሰማ እንዲህም ሆነ የሚለው ሀረግ የተጠቀመው በታሪኩ ሁለተኛውን ክስተት ለማመልከት ነው (አዲስ ክስተት ስለማስታወቅ ይመልከቱ)
የዮሴፍ ጌታ ይህ ጲጥፋራን ያመለክታል::
ይህን ነገር እንዲህ ብላ ነገረችው
“እኛ” የሚለው ቃል ጲጥፋራን ሚስቱንና ሌሎች በቤት ውስጥ ያሉትን ጠቃልላል (ሁሉ አቀፍ እኛን ይመልከቱ)
መሣቂያ ሊያደርገኝ ወደ እኔ ገባ መሣለቂያ የሚለው ቃል ሊይዘኝና ከእኔ ጋር ሊተኛ የሚለውን አባባል በንኀብነት ወይም አንድን ነገር ለዘብ ባለ በተዘዋዋሪ መንገድ የሚገለጽ ነው:: አት “ወዳለሁበት ገባ አስገድዶ ከእኔ ጋር ሊተኛ ሞከረ” (ንኀብነት ወይም አንድን ነገር ለዘብ ባለ በተዘዋዋሪ መንገድ የሚገለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)
“ከዚያም” የጲጥፋራ ሚስት ይህን ሀረግ የተጠቀመችው ዮሴፍ ከእርስዋ ጋር ለመተኛት መሞከሩን ለእርሱ የሚትነግረውን የታሪኩን ሁለተኛውን ክስተት ለማመልከት ነው::(አዲስ ክስተት ስለማታወቅ ይመልከቱ)
ወዲያው ሮጦ ከቤት ወጣ
“እንዲህም ሆነ” የሚለው ሀረግ በታሪኩ አዲስ ክስተት መጀመሩን ለማመልከት ተጠቅሞአል (አዲስ ክስተት ስለማስታወቅ ይመልከቱ)
የዮሴፍ ጌታ ይህ ጲጥፋራን ያመለክታል ይህ መረጃ ግልጽ ሊደረግ ይችላል አት የዮሴፍ ጌታ ጲጥፋራ
ጲጥፋራ እጅግ ተቈጣ
ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል አተ ንጉሡ እስረኞችን ያኖረበት ቦታ ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ
ዮሴፍ በዚያ ቆየ
እግዚአብሔር ለዮሴፍ ተጠነቀቀለት እናም ቸር ነበረ:: “ነገር ግን እግዚአብሔር ለዮሴፍ ቸር ነበር” ወይም “እግዚአብሔር ዮሴፍን ተንከባከበ” (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)
“ታማኝነት” የሚለው ረቂቅ ስም “ታማኝ” ወይም “በታማኝነት” ሊገለጽ ይችላል:: አት ከእርሱ ጋር ለገባው ቃል ኪዳን ታማኝ ነበር ወይም በታማኝነት ወደደው (ረቂቅ ስሞች ይመልከቱ)
ይህም እግዚአብሔር የወህኑ ቤት አዛዥ ዮሴፍን እንዲቀበለውና እንዲንከባከበው አደረገው አት እግዚአብሔር የእስር ቤቱ አዛዥ በዮሴፍ እንዲደሰት አደረገው (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)
“የእስረኞች አስተዳደር” ወይም “በእስር ቤቱ ኃላፊነት የተሰጠው”
እዚህ “እጅ” የሚለው የዮሴፍን ኃይል/አቅም ወይም ታማኝ ኃላፊነት ይወክላል”” አት “ዮሴፍን አለቃ አደረገው” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)
“ዮሴፍ በዚያ ለሚደረገው ነገር ሁሉ ኃላፊ ነበር”
ይህ እግዚአብሔር እንዴት እንደረዳውና እንደመራው የሚያመለክት ነው፡፡ አት “እግዚአብሔር ዮሴፍን ስለመራው” (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)
ዮሴፍ የሚያደርገውን ሁሉ እግዚአብሔር ያሳካለት ነበር