Genesis 35

Genesis 35:1

ወደ ቤተል ውጣ

ውጣ የሚለው ቃል የተጠቀመው ቤቴል ከሴኬም በከፍታ ላይ ስለሚገኝ ነው

በዚያ መሠዊያ ሥራ

እግዚአብሔር ስለራሱ በሶስተኛ ሰው መንገድ ይናገራል:: አት: “ለእኔ ለአምላክህ መሠዊያ ሥራ” (እንደ አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ ሰው መግለጽን ይመልከቱ)

ለቤቱ ሰዎች እንዲህ አላቸው

ለቤተሰቡ እንዲህ አላቸው

በእናንተ ዘንድ ያሉትን ባዕዳን አማልእክት አስወግዱ

“ጣዖታትን አስወግዱ” ወይም “ሐሰተኞች አማልእክትን አስወግዱ”

ራሳችሁን አንጹ ልብሳችሁን ለውጡ

ይህ እግዚአብሔርን ለማምለክ ከመቅረብ በፊት በአካላዊና ሥነምግባራዊ ሕይወት ራስን የማንጻት ልምድ ነበር

ልብሳችሁን ለውጡ

አድስ ልብሶችን መልበስ ወደ እግዚአብሔር ከመቀረባቸው በፊት ራሳቸውን ንጹህ የማድረጋቸው ምልክት ነበር (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)

በመከራዬ ቀን

በመከራዬ ጊዜ ወይም በጭንቀተ ጊዜ

Genesis 35:4

ስለዚህ ሰጡት

“ሁሉም የያዕቆብ ቤት ሰጠ” ወይም “የያዕቆብ ቤተሰብና አገልጋዮቻቸው ሰጡት”

በእጃቸው ያሉትን

እዚህ “በእጃቸው ያሉት” የእነርሱ የሆኑትን ይወክላል:: አት: “ሀብታቸው የሆኑትን ወይም ያላቸውን” (ተመሣሣይ ምትክ ቃላት የመጠቀም ዘይቤ ይመልከቱ)

የጆሮ ጉትቾቻቸውን

ጉትቾቻቸውን ተገቢ ትርጉሞች እነሆ 1 የጆሮቻቸውን ወርቅ ብዙ ጣዖታትን ሊሠሩ ሊጠቀሙ ይችላሉ 2 እነዚህ ጉትቾች የሴኬም ከተማ ሰዎችን በተዋጉና ሁሉን ሰዎች በገደሉ ጊዜ የበዘበዙአቸው ናቸው:: ጉትቾች ስለኃጢአታቸው የሚያውሱ ይሆናሉና::

በዙሪያው ባሉ ከተሞች ሁሉ እግዚአብሔር ድንጋጤ ለቀቀባቸው

ያዕቆብንና ቤተሰቡን የከተሞች ሰዎች እንዲደነግጡ እግዚአብሔር ያደረገው ድንጋጤ እንደ አንድ ነገር በከተሞች እንደወደቀ ተደርጐ ተገልጾአል:: “ድንጋጤ” የተባለው ረቂቅ ስም እንደ “ፍርሃት” ሊገለጽ ይችላል:: አት: “እግዚአብሔር በዙሪያው ያሉ የከተሞች ሰዎች ያዕቆብንና በቤተሰቡን እንዲፈሩ አደረገ” ዘይቤያዊ አነጋገርና ረቂቅ ስሞችን ይመልከቱ

በከተሞች ላይ

“ከተሞች” በከተሞች የሚኖሩ ሰዎችን ይወክላሉ::

የያዕቆብ ወንዶች ልጆች

ከያዕቆብ ቤተሰብ ማንም እንዳልተጠቃ ይገልጻል ነገር ግን የያዕቆብ ሴት ልጅ ከተደፈረች በኋላ ስምዖንና ሌዊ የሴኬምን ከነዓናዊያን ዘመዶችን አጠቁአቸው በዘፍረት 34:3ዐ ያዕቆብ ሊበቀሉ ይፈልጉ ይሆናል ብሎ ፈርቶአል አት የያዕቆብ ቤት ወይም የያዕቆብ ቤተሰብ (ግምታዊ እውቀት ወይም ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)

Genesis 35:6

ሎዛ

ይህ የከተማ ስም ነው:: በዘፍጥረት 28 19 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)

ኤል ቤቴል

ተርጓሚዎች የሚከተለውን የግርጌ ማስታወሻ ሊጨምሩ ይችላሉ፡፡ “ኤል ቤተል የሚለው ስም የቤተል አምላክ ማለት ነው” (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)

እግዚአብሔር የተገለጠለት በዚህ ቦታ ነበር

እግዚአብሔር ራሱን ለያዕቆብ ያስታወቀበት በዚህ ቦታ ነበር

ዲቦራ

ይህ የአንዲት ሴት ስም ነው ስምችን ስለመተርጐም ይመልከቱ

የርብቃ ሞግዚት

ሞግዚት የሌላ ሴት ልጅን የሚትንከባከብ ሴት ማለት ነው ሞግዚት እጅግ የተከበረችና በቤተሰብ ዘንድ ተቀባይነት ያላት ነች

ከቤተል ዝቅ ብሎ …. ተቀበረች

“ዝቅ ብሎ” የሚለው ሀረግ የተጠቀመው እርስዋ የተቀበረችው ቦታ ከፍታ ከቤተል ዝቅ ብሎ ስለሚገኝ ነው::

አሎንባኩት

ተርጓሚዎች የሚከተለውን የግርጌ ማስታወሻ ሊጨምሩ ይችላሉ፡፡ “አሎንባኩት የሚለው ስም ለቅሶ ያለበት ዋርካ ዛፍ ማለት ነው” (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)

Genesis 35:9

ያዕቆብ ከጳዳን አራም በተመለሰ ጊዜ

በቤተል እንደነበሩ ግልጽ ማድረግ ይቻላል አት ያዕቆብም ከጳዳን አራም ከተመለሰ በኋላ በቤተል በነበረበት ጊዜ (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)

ባረከውም

በረከት ለአንድ ሰው መልካም ነገር እንዲደረግለትና በዚያው ሰው ላይ የረከት ቃል መናገር ነው

ከእንግዲህ ያዕቆብ ተብለህ አትጠራም

ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መንገድ ሊተረጐም ይችላል:: አት: “ስምህ ያዕቆብ አይባልም” (ተሻጋሪ ወይም የማይሻገር የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)

Genesis 35:11

እግዚአብሔር እርሱን እንዲህ አለው

እግዚአብሔር ያዕቆብን እንዲህ አለው

ብዛ ተባዛ

ብዙ ልጆች እንዲኖሩት ያዕቆብ ብዙ ልጆችን እንዲወልድ እግዚአብሔር ተናገረው ብዛ የሚለው እንዴት መባዛት እዳለበት ይገልጻል በዘፍጥረት 1:22 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ (ድርብ ቃላትና ፈሊጣዊ ንግግር ይመልከቱ)

ሕዝብና የሕዝቦች ማኀበር ከአንተ ይወጣሉ

እዚህ ሕዝብ እና ሕዝቦች የያዕቆብ ዘሮች እነዚህን ሕዝቦች እንደሚመሠርቱ ነው:: (ተመሣሣይ ምትክ ቃላት የመጠቀም ዘይቤ ይመልከቱ)

እግዚአብሔር ከእርሱ…. ወደ ላይ ወጣ

ወደ ላይ ወጣ የተጠቀመው ከምድር ከፍ ብሎ እግዚአብሔር እንደምኖር ለመግለጽ ነው:: አት: “እግዚአብሔር ተለየው”

Genesis 35:14

ሐውልት

ይህ በጫፉ መከሎ/ቅርጽ ያለው ትልቅ ድንጋይ ለመታሰቢያነት የቆመ ሐውልት ነው

የመጠጥ መስዋዕትንም በእርሱ ላይ አፈሰሰ ዘይትንም አፈሰሰበት

ይህም ሐውልቱን ለእግዚአብሔር የመሰደስ ምልክት ነው (ምልክታዊ ድርጊት ይመልከቱ)

በቴል

ተርጓሚዎች የሚከተለውን የግርጌ ማስታወሻ ሊጨምሩ ይችላሉ፡፡ “በቴል የሚለው ስም የእግዚአብሔር ቤት ማለት ነው” (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)

Genesis 35:16

ኤፍራታ

ይህ የቤተልሔም ከተማ ሌላው ስም ነው

በከባድ ምጥ ውስጥ ሳለች

ምጡ አስጨንቆአት ሳለ

አዋላጅ

አንድ ሴት ልጅን በሚትወልድበት ጊዜ የሚታግዝ ሴት

ስትሞት ነፍስዋ በሚትወጣበት ጊዜ

“ነፍስ መውጣት” አንድ ሰው በሚሞትበት ጊዜ የመጨረሻ እስትንፋስ ማለት ነው፡፡ አት “ከመሞትዋ በፊት በመጨረሻዋ እስትንፋስ ጊዜ” (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)

ቤንኦኒ

ተርጓሚዎች የሚከተለውን የግርጌ ማስታወሻ ሊጨምሩ ይችላሉ፡፡ “ቤንኦኒ የምለው ስም የጭንቀቴ ልጅ ማለት ነው” (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)

ብንያምን

ተርጓሚዎች የሚከተለውን የግርጌ ማስታወሻ ሊጨምሩ ይችላሉ፡፡ “ብንያምን የምለው ስም የቀኝ እጄ ልጅ ማለት ነው” የቀኝ እጅ የሚለው ሀረግ ልዩ የሚወደድ ቦታ ማለት ነው::

ተቀበረች

ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊተረጐም ይችላል:: አት “እነርሱ ቀበሩአት” (ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)

በሚወስድ መንገድ

በሚወስደው መንገድ

እስከዛሬም የራሔል መቃብር ምልክት ይሄው ሐውልት ነው

ይህ እስከዛሬም የራሔል መቃብር ምልክት ነው

እስከዛሬ

እስካሁን ጊዜ ይህ ጸሐፊው፤ ይህ መልእክት የጻፈበትን ጊዜ ያመለክታል፡፡

Genesis 35:21

እስራኤልም ጉዞውን በመቀጠል

የእስራኤል ቤተሰብና አገልጋዮቹ ከእርሱ ጋር እንደነበሩ ይገልጻል የዚህ ሙሉ ትርጉም ግልጽ ሊደረግ ይችላል:: (ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)

ባላ

የራሔል ሴት አገልጋይ ስም ነው:: በዘፍጥረት 29:29 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ::

ያዕቆብ አሥራ ሁለት ወንዶች ልጆች ነበሩት

ይህ ዐረፍተ ነገር በሚከተሉት ቁጥሮች የሚቀጥለውን አድስ አንቀጽ ይጀምራል

አሥራ ሁለት ወንዶች ልጆች

12 ወንዶች ልጆች

Genesis 35:23

ባላ

የራሔል ሴት አገልጋይ ስም ነው:: በዘፍጥረት 29:29 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)

Genesis 35:26

ዘለፋ

የልያ ሴት አገልጋይ ስም ነው:: በዘፍጥረት 29:24 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)

በጳዳን አራም የተወለዱ ነበሩ

ይህ በከነዓን ምድር በቤተልሔም አጠገብ የተወለደውን ብንያምን እንደማያካትት ይናገራል:: አብዛኛዎቹ የተወለዱት በጳዳን አራም ስለሆነ ይህንኑን ይጠቅሳል:: የዚህ ሙሉ ትርጉም ግልጽ ሊደረግ ይችላል:: አት: “በከነዓን ምድር ከተወለደው ከብንያምን በስተቀር በጳዳን አራም የተወለዱለት” (ግምታዊ እውቀት ወይም ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)

ያዕቆብ ወደ ይስሐቅ መጣ

መጣ የተባለው ሄዴ በሚለው ሊተካ ይችላል (ሄዴ እና መጣ ይመልከቱ)

መምሬ

የሔብሮን ከተማ ሌላ ስምዋ ነው የአብርሃም ወዳጆች በኖሩበት በመምሬ ስም ተጠርቶ ይሆናል በዘፍጥረት 13 18 ይህን እንዴት አንደተረጐሙ ይመልከቱ (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)

ቅርያትአርባቅ

ይህ የከተማ ስም ነው በዘፍጥረት 23 2 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)

Genesis 35:28

መቶ ሰማንያ ዓመት

18ዐ ዓመት (ቁጥሮችን ይመልከቱ)

ይስሐቅም ነፍሱን ሰጠ ሞተም

ይስሐቅም የመጨረሻውን እስትንፋስ ሰጠ ሞተም እንትንፋሱን ሰጠ/ነፍሱን ሰጠ ወይም ሞተ የሚሉ ሀረጐች በመሠረቱ አንድ ትርጉም አላቸው:: በዘፍጥረት 25:8 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ:: አት: “ይሥሐቅም ሞተ” (ድርብ ቃላት ይመልከቱ)

ነፍሱን ሰጠ

ይህ አንድ ሰው መሞቱን ትሁትና መንገድ የሚገልጽ ነው:: በዘፍጥረት 25:8 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ:: (ንኀብነት ለዛ ባለ ወይም በተዘዋዋሪ አንድን ነገር የመግለጽ ዘይቤያዊ አባባል ይመልከቱ)

ወደ ወገኖቹ ተከማቸ/ተሰበሰበ

ይስሐቅ ከሞተ በኋላ ከዚህ በፊት የሞቱ ወገኖች ነፍስ ወዳለበት ቦታ ነፍሱ ሄደች ማለት ነው ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊተረጐም ይችላል አት የሞቱትን የቤተሰብ አባላትን ተቀለቀለ ማለት ነው:: (ፈሊጣዊ አነጋገር እና ተሻጋሪና የማይሻገር ግሥ የያዙ ዐረፍተ ነገሮችን ይመልከቱ)

አርጅቶ እድሜ ጠግቦ

አረጅቶ እና እድሜ ጠግቦ የሚሉ ሀረጐች በመሠረቱ ተመሣሣይ ትርጉም አላቸው:: አበክረው የሚናገሩት ይስሐቅ ብዙ ዓመታትን እንደኖረ ነው:: አት: “ብዙ ዓመታትን ኖሮ ከአረጀ በኋላ” (ድርብ አባባል ይመልከቱ)